Error
  • JUser: :_load: Unable to load user with ID: 62
Saturday, 18 August 2012 13:35

“ምወዳዕታ መአልቲ” እና “ማጆሪስ” ለንባብ በቁ “ምስጢራዊ ማህተም” ማክሰኞ ይመረቃል

Written by 
Rate this item
(1 Vote)

በጋዜጠኛ ዓዲስ ዓለም ሃጎስ በትግርኛ የተፃፈው “ምወዳዕታ መአልቲ” የአጫጭር ልቦለዶች መድበል ከዛሬ ጀምሮ በመቀሌ ከተማ ለንባብ እንደሚበቃ ፀሃፊው ገለፀ፡፡ በመቀሌ ከተሠራጨ በኋላ በአዲስ አበባና በሌሎች ክልሎች የሚሰራጨው ባለ 104 ገፅ መፅሐፍ ለገበያ የቀረበበት ዋጋ 30 ብር ነው፡፡ የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ባልደረባ የሆነው ጋዜጠኛ ዓዲስ ዓለም ካሁን ቀደም “ወይዘሪት ኢትዮጵያ” የተሰኘ መፅሐፍ ለንባብ ማብቃቱ ይታወቃል፡፡ ይህ በዚህ እንዳለ በጥላሁን ብርሃኑ የተዘጋጀው “ማጆሪስ” ረዥም ልቦለድ ባሳለፍነው ሳምንት ለንባብ በቃ፡፡ መፅሐፉ ዛሬ ከጧቱ 3 ሰዓት በኢትዮጵያ ብሔራዊ ትያትር ይመረቃል፡፡

ደራሲው መታሰቢያነቱን ለኢትዮጵያ ሰላምና ብልፅግና ሕይወታቸውን ሙሉ ለጣሩ ሰዎች ባደረገው መፅሐፍ የጀርባ ሽፋን ላይ አስተያየት ከሰጡ ግለሰቦች መካከል አርቲስት ስዩም ተፈራ መፅሐፉን “ልብ ሰቃይ፣ ፈጣንና የሥለላ ታሪኮች የተሰናሰሉበት” በማለት አስተያየቱን ሲሰጥ መፅሐፉን ማንበባቸውን የተናገሩት ፕሮፌሰር በየነ ጴጥሮስ “የመቻቻል ፖለቲካን አስፈላጊነት የገለፀ” ብለውታል፡፡ 270 ገፆች ያሉት መፅሐፉ ለሀገር ውስጥ በ39 ብር በውጭ ሀገራት በ19 ዶላር ለገበያ ቀርቧል፡፡ በሌላም በኩል “ሚስጢራዊ ማህተም” አዕምሮአዊ ልቦለድ መጽሐፍ ማክሰኞ ከቀኑ 10 ሰዓት በኢትዮጵያ ብሔራዊ ቤተመዛግብትና ቤተመፃሕፍት አዳራሽ ይመረቃል፡፡ 202 ገፆች ያሉትን መፅሐፍ ያዘጋጁት ገብረሥላሴ አፅብሃ (ባዜን) ናቸው፡፡ የመፅሐፉ ዋጋ 35 ብር ነው፡፡

 

 

Read 1270 times Last modified on Saturday, 18 August 2012 13:46