Error
  • JUser: :_load: Unable to load user with ID: 62
Saturday, 11 August 2012 12:23

“ቪ.አይ.ፒ” ነገ ይመረቃል

Written by 
Rate this item
(0 votes)

በፆታ ለውጥ ላይ የተሰራው ፊልም ሊመረቅ ነው  ፣   “የኔታ” ፊልም በደቡብ አፍሪካ ይመረቃል

ብሉ ስካይ የፊልም ሥራ ድርጅት አምስት አመታት ፈጅቶብኛል ያለውን በፆታ ለውጥ ላይ ያተኮረ ፊልም ሊያስመርቅ ነው፡፡ “የሲኦል ሙሽሮች” በሚል ርእስ የሚቀርበው የ105 ደቂቃ ፊልም የሚመረቀው ነሀሴ 14 በኢትዮጵያ ብሔራዊ ትያትር ሲሆን ካለፈው እሁድ ጀምሮ በአጎና ሠራዊት፣ በሴባስቶፖል በዓለም፣ በሻሎም፣ በካፍደም፣ በአምፒር ሲኒማ ቤቶች እና በሐገር ፍቅር ትያትር ቤት መታየት ጀምሯል፡፡

አዘጋጆቹ ልብ አንጠልጣይ ኤፒክ ነው ባሉት ፊልም ዳዊት ነፀረአብ፣ ኤፍሬም አደፍርስ፣ ኤልያስ ማዳ፣ ሳባ ጌታቸው እና ሌሎች ተውነዋል፡፡ ፊልሙን ያዘጋጀው ግርማ በቀለ ከምሲ ነው፡፡ በሌላም በኩል የድምፃዊት፣ ገጣሚና ተዋናይት ሩታ አርአያ “የኔታ” የተሰኘ ፊልም በደቡብ አፍሪካ ፖርት ኤልዛቤት ከተማ፣ ነሐሴ 12 ቀን 2004 ዓ.ም ከቀኑ በ10 ሰዓት በግራንድ ሆቴል እንደሚመረቅ ተገለፀ፡፡ በፊልሙ ላይ ከ16 በላይ ተዋናዮች የተሳተፉ ሲሆን ፍላይ ፒ.ዲ.ቤይ ቲቪ በተሰኘ ታዋቂ የፊልም ኩባንያ መሰራቱ ታውቋል፡፡ በዕውቅ እንግሊዛዊ የካሜራ ባለሙያ የተቀረፀ ነው የተባለውን ፊልም ሰርቶ ለማጠናቀቅ አንድ ዓመት ፈጅቷል፡፡ የፊልሙ ዳይሬክተርና ፕሮዲዩሰር ሩታ አርአያ ለዝግጅት ክፍላችን እንደገለፀችው፤ ፊልሙ በቅርቡ በሃገር ውስጥ ተመርቆ መታየት ይጀምራል፡፡ በ“ሔልዳን ፊልም ፕሮዳክሽን የተሰራው “ቪ አይ ፒ” አስቂኝ ምፀታዊ ፊልም ነገ ይመረቃል፡፡ ዶ/ር ናትናኤል ብርሃኑ እና ዘውዱ ዳርቻ ፕሮዲዩስ ያደረጉትን ፊልም ኤርምያስ ግርማ ጽፎት አየለ አበበ እና አብዱልከሪም ጀማል አዘጋጅተውታል፡፡ ሸዋፈራሁ ደሳለኝ፣ መኮንን ላዕከ፣ ድርብወርቅ ሰይፉ፣ ፍሬሕይወት ባህሩ፣ ሳሙዔል ተስፋዬ እና ሌሎች ተውነውበታል፡፡ የ100 ደቂቃ ፊልሙን ሠርቶ ለማጠናቀቅ 14 ወራት ፈጅቷል፡፡

 

 

 

Read 1755 times Last modified on Saturday, 11 August 2012 12:26