የድምፃዊት፣ ገጣሚና ተዋናይት ሩታ አርአያ “የኔታ” የተሰኘ ፊልም በደቡብ አፍሪካ ፖርት ኤልዛቤት ከተማ፣ ነሐሴ 12 ቀን 2004 ዓ.ም ከቀኑ በ10 ሰዓት በግራንድ ሆቴል እንደሚመረቅ ተገለፀ፡፡ በፊልሙ ላይ ከ16 በላይ ተዋናዮች የተሳተፉ ሲሆን ፍላይ ፒ.ዲ.ቤይ ቲቪ በተሰኘ ታዋቂ የፊልም ኩባንያ መሰራቱ ታውቋል፡፡ በዕውቅ እንግሊዛዊ የካሜራ ባለሙያ የተቀረፀ ነው የተባለውን ፊልም ሰርቶ ለማጠናቀቅ አንድ ዓመት ፈጅቷል፡፡ የፊልሙ ዳይሬክተርና ፕሮዲዩሰር ሩታ አርአያ ለዝግጅት ክፍላችን እንደገለፀችው፤ ፊልሙ በቅርቡ በሃገር ውስጥ ተመርቆ መታየት ይጀምራል፡፡