በወጣት ከያንያን እየተዘጋጀ የሚቀርበው “ግጥምን በጃዝ” ወርሃዊ የግጥምና የሙዚቃ ዝግጅት በመጪው ሰኞ እና ረቡዕ ምሽት እንደሚቀርብአዘጋጆቹ አስታወቁ፡፡ የ”ግጥምን በጃዝ” ፒያሳ በሚገኘው ጣይቱ ሆቴል በየሁለት ሳምንቱ ሰኞ መቅረብ የጀመረ ሲሆን ከነገ ወዲያም ሁለተኛ ዝግጅቱ በአቢሲኒያ ሳውንድ የሙዚቃ ባንድ በመታጀብ እንደሚቀርብ ለማወቅ ተችሏል፡፡ ላለፉት 12 ወራት በዋቢ ሸበሌ ሆቴል ሲቀርብ የነበረው ዝግጅት በረቡዕ ዝግጅት አንዲት አርቲስት የአንድ ሰው ተረትን በድራማ የምታቀርበውን ጨምሮ አርቲስት ግሩም ዘነበ፣ ሰሎሞን ሳህለ፣ ምልዕቲ ኪሮስ፣ ምህረት ከበደ፣ ደምሰው መርሻና ሌሎች የግጥም እና የወግ ዝግጅቶቻቸውን ያቀርባሉ፡፡ የዝግጅቶቹ መግቢያ በነፍስ ወከፍ 50 ብር ነው፡፡