Saturday, 26 September 2020 00:00

ለሐበሻ ቢራ “ቅዳሜ” የተሰኘ አዲስ ምርቱን ዛሬ ያቀርባል

Written by 
Rate this item
(2 votes)

  የደመራ ስጦታ ለደንበኞች


           ሃበሻ ቢራ “ቅዳሜ” የተሰኘ አዲስ የቢራ ምርቱን ከዛሬ ጀምሮ ለተጠቃሚዎች እንደሚያቀርብ አስታወቀ፡፡
ከ8ሺ በላይ የአክሲዮን ባለድርሻ ኢትዮጵያውያን ተመስርቶ፣ በ2007 “ሐበሻ ቢራ” እና “ንጉስ” የተባሉ የቢራ ምርቶችን ለገበያ ማቅረብ የጀመረው ሐበሻ ቢራ፤ አዲሱን “ቅዳሜ” የተሰኘ ምርቱን ዛሬ በደመራ እለት ለደንበኞቹ ያቀርባል፡፡
ኩባንያው ለተጠቃሚዎች ይዞ የቀረበው አዲሱ “ቅዳሜ” የተሰኘው የቢራ ምርት ከፍተኛ ጥራት ያለው እርካታን የሚሰጥ ጣዕም ያለው ምርት መሆኑን ኩባንያው በመግለጫው አስታውቋል፡፡
ሀበሻ ቢራን ለገበያ ማቅረብ ከጀመረ 5 አመታት ያስቆረጠውና ከአልኮል ነፃ የሆነውን ንጉስ የተሰኘውን መጠጥ ደግሞ ማቅረብ ከጀመረ ሁለት አመታት የሆኑት ኩባንያው ምርቶቹን ከሀገር ውስጥ በተጨማሪ በተለያዩ የአውሮፓ ሀገራት እና አሜሪካ እየቀረበ መሆኑን አስታውቋል፡፡  

Read 2993 times