“ፕሪንሰስ ኦፍ ቻይና” ዘፈን የተባለውን ዜማ ከሪሃና ጋር መስራታቸውን እንደወደዱት ግን ተናግሯል፡፡ ለ”ኮልድ ፕሌይ” የሙዚቃ ባንድ አምስተኛ አልበም የሆነውን “ማይሎ ዛይሎቶ” ለማስተዋወቅ ዛሬና ነገ በማንችስተር ሲቲ ስታዲየም ደማቅ የሙዚቃ ኮንሰርት የሚቀርብ ሲሆን የመግቢያ ትኬቱ በ90 ደቂቃ ተሸጦ ማለቁ የባንዱን ተወዳጅነት ይጠቁማል ተብሏል፡፡ ኮንሰርቱን 50ሺ ገደማ ተመልካቾች እንደሚታደሙት ይጠበቃል፡፡ ኮልድ ፕሌይ በሚያቀርበው ኮንሰርቱ የባንዱ መሪ ድምፃዊው ክሪስ ማርቲን፤ ሁለቱ ጊታሪስቶች ጋይ ቤሪማንና ጆኒ ቢኪላንድ እንዲሁም ድራመሩ ዊል ሻምፒዮን ይጫወታሉ፡፡ከዓመት በፊት ለገበያ የቀረበው የባንዱ አምስተኛ አልበም በአሜሪካ 1 ሚሊዮን ቅጂዎች ሲሸጡ፤ በእንግሊዝ ደግሞ ከ900ሺ በላይ ቅጂዎች ተሸጠዋል፡፡ የ “ኮልድ ፕሌይ” ቡድን ሰባት የግራሚ አዋርድ የተሸለሙ ሲሆን በመላው ዓለም ከ50 ሚሊዮን በላይ የአልበማቸውን ቅጂዎች ሸጠዋል፡፡