Saturday, 13 July 2019 11:40

1.3 ቢ. ዜጎች በከፋ ድህነት ውስጥ ይገኛሉ ተባለ

Written by 
Rate this item
(1 Vote)

በአለማችን 101 አገራት 1.3 ቢሊዮን ያህል ዜጎች በከፋ ድህነት ውስጥ እንደሚገኙ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የልማት ፕሮግራም ከትናንት በስቲያ ባወጣው አለማቀፍ የድህነት ሁኔታ አመላካች ሪፖርት አስታውቋል፡፡
ድርጅቱ አነስተኛ፣ መካከለኛና ከፍተኛ ገቢ ባላቸው 101 የአለማችን አገራት ውስጥ የዜጎችን ገቢ፣ የጤና አገልግሎት፣ የስራ ዕድልና አጠቃላይ የኑሮ ሁኔታ በተመለከተ የሰራውን ጥናት መሰረት አድርጎ ይፋ ባደረገው ሪፖርት እንዳለው፣ በአገራቱ  የሚገኙ 1.3 ቢሊዮን ዜጎች፣ በተደራራቢ የከፋ ድህነት ውስጥ መዘፈቃቸውን ለማረጋገጥ ተችሏል፡፡
ድህነት በሁሉም አገራት እንደሚታይ የጠቆመው ጥናቱ፤ በአገራት ዜጎች መካከል ሰፊ የኑሮ ደረጃ ልዩነት መኖሩን ያመለከተ ሲሆን፣ ከአጠቃላዩ ድሃ ህዝብ መካከል 84.5 በመቶ ያህሉ ከሰሃራ በታች ባሉ የአፍሪካ አገራትና በደቡብ እስያ አገራት ውስጥ እንደሚገኙም ገልጧል፡፡
ጥናቱ በተደረገባቸው አገራት ከሚገኙት 1.3 ቢሊዮን ያህል ድሃ ዜጎች ውስጥ ከግማሽ በላይ የሚሆኑት ወይም 663 ሚሊዮን ያህሉ ከ18 አመት በታች የሚገኙ ህጻናት መሆናቸውንና ከእነዚህ ህጻናት መካከል 85 በመቶ ያህሉ ከሰሃራ በታች ያሉ የአፍሪካ አገራትና የደቡብ እስያ አገራት ዜጎች መሆናቸውንም ሪፖርቱ አመልክቷል፡፡


Read 3090 times