Sunday, 16 June 2019 00:00

አሜሪካዊቷ የአለም አገራትን በሙሉ በመጎብኘት ታሪክ ሰርታለች

Written by 
Rate this item
(0 votes)

የ21 አመቷ አሜሪካዊት ሌክሲ አልፎርድ በለጋ ዕድሜዋ ሁሉንም የአለማችን አገራት በመጎብኘት አዲስ ክብረ ወሰን ማስመዝገቧን ፎርብስ መጽሄት ከሰሞኑ ዘግቧል፡፡ላለፉት ተከታታይ አመታት የአለማችንን አገራት ከዳር እስከ ዳር በማዳረስ ተጠምዳ የኖረችውና ባለፈው ሳምንት ሰሜን ኮርያ የገባችው ሌክሲ፣ በለጋ ዕድሜዋ ሁሉንም የአለማችን አገራት የጎበኘች ሴት የመሆን ዕቅዷን በድል በማጠናቀቅ በአለም የድንቃ ድንቅ መዝገብ ላይ ሰፍራለች፡፡የአለማችንን 196 አገራት በሙሉ የመጎብኘት ዕቅድ ይዛ የተነሳችው ገና ህጻን ሳለች ጀምሮ እንደነበር የተነገረላት ሌክሲ፣ እ.ኤ.አ በ2013 ላይ በ24 አመቱ ሁሉንም አገራት ከጎበኘው አሜሪካዊው ጄምስ አስኪዝ ክብረወሰኑን ከመንጠቋ በተጨማሪ አገራቱን በአጭር ጊዜ ውስጥ ጎብኝታ በመጨረስም ታሪክ መስራቷን ዘገባው አመልክቷል፡፡ ካሊፎርኒያ ውስጥ የአስጎብኝ ድርጅት ባለቤት በሆነ ቤተሰብ ውስጥ ያደገችው ሌክሲ፣ በለጋ እድሜዋ ከቤተሰቦቿ ጋር ወደተለያዩ አገራት የመጓዝ ዕድል እንዳገኘችና የ18 አመት ወጣት እያለች 72 የአለማችን አገራትን እንደጎበኘች ያስታወሰው ዘገባው፣ ከሶስት አመታት በፊት ግን ቀሪዎቹን 124 አገራት በማዳረስ ክብረወሰኑን ለመስበር በትጋት አለምን መዞር መጀመሯን አመልክቷል፡፡

Read 1199 times