ለቤተ መፃህፍቱ አራተኛ የሆነው ዝግጅት ከ12 እስከ 17 አመት ያሉ ታዳጊዎች የተካተቱበት ነው፡፡ ስለ ዝግጅቱ ቀጣይነት ከዝግጅት ክፍላችን የተጠየቀው የቤተመፃህፍቱ ባለቤት እና ሥራ አስኪያጅ ደራሲ እንዳለጌታ ከበደ የቦታ እና የአቅም ችግር ባይኖርብን ዝግጅቱ በየወሩ ይሆን ነበር ብሎናል፡፡
ዛጐል ቤተመፃህፍት ከእሸት ECYDO ጋር በመተባበር ያሰናዱት የሕፃናት የሥነፅሁፍ ዝግጅት ባለፈው ቅዳሜ ጧት በሩስያ ሳይንስ እና ባህል ማዕከል ፑሽኪን አዳራሽ ቀረበ፡፡ ደራሲ ኃይለመለኮት መዋዕል የልጆች እንካሰላንትያ ባቀረበበት ዝግጅት ገጣሚና ተዋናይ ሜሮን ጌትነት አርቲስትነትን ለልጆች በሚገባ ቋንቋ ገለፃ አድርጋለች፡፡ የዝግጅቱ የክብር እንግዳ በርካታ የልጆች መፃህፍት በማዘጋጀት የሚታወቀው ደራሲ ተሾመ ብርሃኑ ነው፡፡ ልጆች የራሳቸውን ትረካዎች፣ ግጥሞችና ድራማ አቅርበዋል፡፡
ለቤተ መፃህፍቱ አራተኛ የሆነው ዝግጅት ከ12 እስከ 17 አመት ያሉ ታዳጊዎች የተካተቱበት ነው፡፡ ስለ ዝግጅቱ ቀጣይነት ከዝግጅት ክፍላችን የተጠየቀው የቤተመፃህፍቱ ባለቤት እና ሥራ አስኪያጅ ደራሲ እንዳለጌታ ከበደ የቦታ እና የአቅም ችግር ባይኖርብን ዝግጅቱ በየወሩ ይሆን ነበር ብሎናል፡፡