Monday, 28 January 2019 00:00

“ሰውነቷ” በእውነተኛ ታሪክ ላይ የተመሰረተ ፊልም ተመረቀ

Written by  ናፍቆት ዮሴፍ
Rate this item
(1 Vote)

ህገ ወጥ የሰዎች ዝውውርን ለመከላከል የሚያስችል ግንዛቤ እንደሚፈጥር የተነገረለት በእውነተኛ ታሪክ ላይ የተመሰረተ “ሰውነቷ” የተሰኘ ፊልም በትላንትናው ምሽት በሃያት ሪጀንሲ ሆቴል ተመርቋል፡፡
በምረቃ ሥነ ስርዓቱ ላይ የተገኙት የአገሪቱ ፕሬዚዳንት ሳህለወርቅ ዘውዴ፤ ህብረተሰቡ ህገ ወጥ የሰዎች ዝውውርን እንዲከላከል መልዕክት ማስተላለፋቸውን ለማወቅ ተችሏል፡፡
ፊልሙን የሰራተኛና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር ከዓለም የሥራ ድርጅት ጋር በመተባበር ያዘጋጀ ሲሆን ዓላማውም በህብረተሰቡ ውስጥ ህገ ወጥ የሰዎች ዝውውርን ለመከላከል የሚያስችል ግንዛቤ በጥበብ አማካኝነት ለማስረፅ ነው ተብሏል፡፡  

Read 5166 times Last modified on Saturday, 26 January 2019 16:05