በገጣሚ ሀብታሙ ገ/መድህን የተፃፉ ከ60 በላይ ግጥሞችን ያካተተው “ትላንት ዛሬ ነገ” የተሰኘ የግጥም መድበል ለንባብ በቃ፡፡
በተለያዩ ርዕሰ ጉዳዮች ላይ የሚያጠነጥኑ ግጥሞችን የያዘው መፅሀፉ፤ ባለፈው ጥቅምት 29 አንጋፋው ድምፃዊ ባህታ ገ/ሕይወትና እውቁ ገጣሚ በላይ በቀለ ወያ በተገኙበት በጅማ ዩኒቨርሲቲ ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት አዳራሽ መመረቁም ታውቋል፡፡ በ72 ገፆች የተመጠነው መፅሀፉ፤ በ35 ብር እየተሸጠ ነው፡፡
Saturday, 18 November 2017 13:27
“ትላንት ዛሬ ነገ” የግጥም መድበል ለንባብ በቃ
Written by ናፍቆት ዮሴፍ
Published in
ኪነ-ጥበባዊ ዜና