Saturday, 26 August 2017 11:36

አድማስ ዩኒቨርሲቲ ዛሬ በቢሾፍቱ ተማሪዎችን ያስመርቃል

Written by 
Rate this item
(0 votes)

 አድማስ ዩኒቨርሲቲ በቢሾፍቱ ካምፓስ ትምህርታቸውን ተከታትለው ያጠናቀቁ ከ500 በላይ ተማሪዎቹን ዛሬ በቢሾፍቱ ተዘራ ሲኒማ አዳራሽ ያስመርቃል፡፡
ከሚመረቁት መካከል 210 ተማሪዎች በድግሪ መርሀ ግብር ትምህርታቸውን ሲከታተሉ የቆዩ ሲሆን ቀሪዎቹ 300 ተማሪዎች ደግሞ በቴክኒክና ሙያ ዘርፎች ስልጠናቸውን የተከታተሉ መሆናቸውን ዩኒቨርሲቲው በላከው መግለጫ አስታውቋል፡፡ ከተመራቂዎቹ መካከል 70 በመቶ የሚሆኑት ሴት ተማሪዎች ናቸው ብሏል-ዩኒቨርሲቲው፡፡
አድማስ ዩኒቨርሲቲ በሶማሌላንድና በፑትላንድ የሚገኙትን ጨምሮ በ10 ካምፓሶች እንዲሁም ከ60 በላይ በሚሆኑ የርቀት ትምህርቱ ማዕከላት እስከዛሬ ድረስ ከ40 ሺህ በላይ ተማሪዎችን ማስመረቁን ገልጿል፡፡
ዩኒቨርሲቲው በዚህ ዓመት በመካኒሳና በመቐለ አዳዲስ ካምፓሶችን ከፍቶ፣ የዲግሪና የቴክኒክና ሙያ መርሀ ግብሮች ስልጠና መጀመሩን ጠቁሞ፣ በቅርቡ በ4 የስልጠና ዘርፎች በማስተርስ ደረጃ ተማሪዎችን ተቀብሎ ለማሰልጠን ዝግጅቱን ማጠናቀቁን አስታውቋል፡፡

Read 1352 times