Saturday, 29 July 2017 11:11

የሬጌው አቀንቃኝ ፕሮቶጄ ዛሬ በላፍቶ ሞል ያቀነቅናል

Written by 
Rate this item
(1 Vote)

    በአውሮፓና በአሜሪካ ከ120 በላይ ስኬታማ የሙዚቃ ኮንሰርቶችን በማቅረብ የሚታወቀው የሬጌው አቀንቃኝ ኦጄኬን ኦሊቨር ወይም በመድረክ ስሙ “ፕሮቶጄ” ዛሬ ምሽት በላፍቶ ሞል ያቀነቅናል። “The Indignation” ተብሎ በሚጠራውና በሰባት ታዋቂ የሙዚቃ ተጫዋች የተደራጀው ሙሉ ባንዱ ታጅቦ የሚያቀነቅነው  የ33 ዓመ ከታወጀ 10 ወር ገደማ ያስቆጠረው የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ ከ5 ቀን በኋላ ይነሳ ይቀጥል የሚታወቅ ሲሆን  ሰማያዊ ፓርቲ በበኩሉ፤የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ ከተነሳ፣ ሐምሌ 30 እና ነሐሴ 7 ቀን 2009 ዓ.ም፣ በአዲስ አበባ ህዝባዊ ስብሰባና ሰላማዊ ሰልፍ ለመጥራት ማቀዱን አስታውቋል፡፡
ፓርቲው ሰሞኑን ባወጣው ወቅታዊ የአቋም መግለጫው፤አስር ወራትን ያስቆጠረው የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ የማብቂያው ጊዜ ከ5 ቀን በኋላ፣ መሆኑን በመጠቆም፣ አዋጁ ለተጨማሪ ጊዜያት እንዳይራዘም መንግስትን ጠይቋል፡፡ አዋጁ ተጥሎ በቆየባቸው ጊዜያት፤ “የዜጎችን ሰብአዊና ዲሞክራሲያዊ መብቶች የጣሰ፣ የፖለቲካ ምህዳሩን ከመቼውም ጊዜ ይልቅ ያጠበበ፣ የሀገሪቱን ኢኮኖሚ እንዲያሽቆለቁል ያደረገና የህዝብን ማህበራዊ መስተጋብሮች የገታ ነበር” ያለው ሰማያዊ፤ “መንግስት ሀገሪቱን አረጋግቻለሁ ስላለ አዋጁን ማራዘም አያስፈልግም፤ ሊነሳ ይገባዋል” ብሏል፡፡ በቅርቡ በሚኒስትሮች ም/ቤት ተወስኖ፣ ለህዝብ ተወካዮች ም/ቤት የቀረበው የኦሮሚያ ክልል በአዲስ አበባ ላይ ያለው ልዩ ጥቅም ረቂቅ አዋጅ፣ የአዲስ አበባና የኦሮሚያ ህዝብ ሳይመክርበት መውጣቱን ፓርቲው ተችቷል፡፡ የግብር አጣጣል ስርዓቱም የዜጎችን ገቢ ያገናዘበ እንዲሆን የጠየቀው ፓርቲው፤ በአጠቃላይ ህዝቡ በአግባቡ ሳይመክርባቸው እየወጡ ያሉ አዋጆች፣ በዜጎች ላይ መደናገጥ እየፈጠሩ በመሆኑ ሊታረሙ  ይገባል ሲል አሳስቧል።
“ሰማያዊ” የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ሊነሳ ይችላል በሚል መተማመን፣ ሐምሌ 30፣ ከጠዋቱ 4 ሰዓት እስከ ቀኑ 9 ሰዓት ሜክሲኮ አደባባይ በሚገኘው የመብራት ሃይል አዳራሽ፣ ህዝባዊ ስብሰባ እንዲሁም ነሐሴ 7፣ መነሻውን ሚኒልክ አደባባይ፣መዳረሻውን መስቀል አደባባይ ያደረገ፣ ሰላማዊ ሠልፍ ለመጥራት ማቀዱን አስታውቋል፡፡ የስብሰባውም ሆነ የሰልፉ አጀንዳዎች፣ በዋናነት እየወጡ ባሉ አዋጆች ላይ እንደሚያተኩር ለአዲስ አድማስ ያስረዱት የፓርቲው የህዝብ ግንኙነት ሃላፊ አቶ አበበ አካሉ፤ሰልፉም ሆነ ስብሰባው የታቀደው የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ ሊነሣ ይችላል በሚል ግምት መሆኑን አስታውቀዋል፡፡
ቱ ፕሮቶጄ፤ ትላንት ከቀኑ 8፡00 ላይ በአምባሳደር ሆቴል ከኮንሰርቱ አዘጋጅ EML ኤቨንት ኦርጋናይዘርስ ጋር በጋራ በሰጠው መግለጫ፤ የዛሬው የላፍቶ ሞል ኮንሰርቱ በአፍሪካ የመጀመሪያው እንደሆነ ገልጿል፡፡ ወደ ኢትዮጵያ ከመምጣቱ በፊት ጣሊያን፣ ስዊድን፣ ጀርመን፣ ፈረንሳይና ስፔይን ትልልቅ ኮንሰርቶችን እንዳቀረበና እዚህ ያለውን ስራ ሲጨርስም ወደ አውሮፓ ተመልሶ ስራውን እንደሚያቀርብ ተናግሯል፡፡
ዘፋኝ ባይሆን ኖሮ ሯጭ ይሆን እንደነበር በመግለጫው የጠቆመው ዘፋኙ፤ አትሌት ሃይሌ ገ/ሥላሴን ጨምሮ ብዙ የኢትዮጵያ አትሌቶችን በስም ጭምር እንደሚያውቅ የተናገረ ሲሆን “አትሌት ጥሩነሽ ዲባባን ከልቤ አደንቃለሁ” ብሏል፡፡ የኢትዮጵያ መንግሥት ሰሞኑን ለራስ ተፈሪያን የትውልደ ኢትዮጵያዊነት መብትና ዕውቅና መስጠቱን በተመለከተ የተጠየቀው ዘፋኙ፡-
“በጣም ትልቅና ታላቅ እድል ነው፡፡ እኛ ወደ ኢትዮጵያ መጥተን መኖር የምንፈልገው ለአገሪቷ ሸክም ለመሆን አይደለም፡፡ አላማ አለን፤ ራዕይ አለን፡፡ ጓዛችንን ጠቅልለን ስንመጣ ከእውቀት፣ ከሰፊ ልምድና ሙያ ጋር ነው፡፡ ኢትዮጵያ መጥተን ልንዝናና ወይም ሳንሰራ ተቀምጠን ለመኖር አይደለም፡፡ ማንም ራስ ተፈሪያን ወደ ኢትዮጵያ ለመምጣት ሲያስብ፣ የራሱን ሀሳብ ይዞ ነው፡፡ ያንን ሀሳብ የሚፈፅመውም ኢትዮጵያን ለመጥቀም ነው” ሲል መልሷል፡፡ከዚህ በፊት ይከሰት የነበረውን ትርምስና ጭንቅንቅ ለማስቀረት ሲባል ተጨማሪ ባሮች በላፍቶ ሞል መዘጋጀታቸውን የጠቆሙት አቶ ኢዩኤል፤ ከቀኑ 10 ሰዓት ጀምሮ ተመልካቾች ወደ አዳራሹ መግባት ይጀምራሉ ብለዋል፡፡ ኮንሰርቱ ቀድመው ትኬት ለገዙ 300 ብር፣ በዕለቱ ለሚገዙ በመደበኛው 500 ብር፣ በቪአይፒ 700 ብር የመግቢያ ዋጋ ተተምኖለታል፡፡


Read 2090 times