2” ሐሙስ ይመረቃሉ ድምፃዊ፣ የዜማና ደራሲ ድምፃዊ ጌትሽ ማሞ ለህዝብ ጆሮ ያበቃቸው ሁለት ነጠላ ዜማዎች
(‹‹ተቀበል 1 እና 2››) የፊታችን ሐሙስ በፍሬንድሺፕ ሆቴል ኤቪ ክለብ ከምሽቱ 3፡00 ጀምሮ ይመረቃል፡፡
“ተቀበል” በተሰኘው ነጠላ ዜማው ከፍተኛ ተቀባይነትን ያገኘው ጌትሽ ማሞ፤ “ተቀበል 2”(እንከባበር) የሚል ነጠላ ዜማውም ተወዳጅነት
ማግኘቱ የተገለፀ ሲሆን የነዚህን ዜማዎች ቪዲዮ ክሊፕ ለማስመረቅ መወሰኑን ረቡዕ ረፋድ ላይ በፍሬንድሺፕ ሆቴል በሰጠው መግለጫ አስታውቋል፡፡ በምርቃት ሥነስርዓቱ ላይ ከ15 በላይ ታዋቂ አርቲስቶች የሙዚቃ ስራዎቻቸውን ያቀርባሉ ተብሏል፡፡
Published in
ኪነ-ጥበባዊ ዜና