Sunday, 25 June 2017 00:00

2800 ኢትዮጵያውያን የቤት ሠራተኞች ወደ ሣኡዲ ይላካሉ ተባለ

Written by 
Rate this item
(5 votes)

ደሞዛቸው በወር 800 ሪያል ይሆናል
ከሁለት ወራት በኋላ 2800 ኢትዮጵያውያንን በቤት ሠራተኝነት ወደ ሣኡዲ አረቢያ ለመላክ የሚያስችል ዝግጅት መጠናቀቁን በጅዳ የሚገኘው ቆንፅላ ፅ/ቤት አረጋግጦልኛል ሲል ሣኡዲ ጋዜጣ ዘግቧል፡፡
150 ያህል ሰራተኛ በአዲስ አበባ ባለ 5 እና ባለ 10 ብር ካርድ እጥረት የተፈጠረው በከተማዋ የካርድ ተጠቃሚዎች በመበራከታቸው መሆኑን ኢትዮ- ቴሌኮም አስታወቀ፡፡ ለካርዶቹ መጥፋት ከተጠቃሚው መብዛት ባሻገር የስርጭት ችግር መኖሩን ለአዲስ አድማስ የጠቆሙት የኢትዮ-ቴሌኮም የኮርፖሬት ኮሚኒኬሽን ኃላፊ አቶ አብዱራሂም አህመድ፤ አከፋፋዮች እጥረት አለ ሲባል አጋጣሚውን ተጠቅመው ዋጋ ለመጨመር ሰው ሰራሽ እጥረት መፍጠራቸውን ገልፀዋል፡፡
በሳምንት 50 ሚሊዮን  የባለ 5 እና 10 ብር ካርዶች ፍጆታ ላይ ይውሉ እንደነበር የጠቆሙት አቶ አብዱራሂም፤ በአሁን ወቅት ከ100 ሚሊዮን በላይ ካርድ እንደሚቀርብ ሰው ሰራሽ እጥረቱን ማሳያም ነው ብለዋል፡፡
ችግሩን በአፋጣኝ ለማቃለል 140 ሚሊዮን ባለ 5 እና 140 ሚሊዮን ባለ 10 ብር ካርዶች በውጭ ሀገር አሳትሞ ወደ ሀገር ውስጥ በማስገባት ላይ መሆኑን የጠቀሱት አቶ አብዱራሂም፤  ችግሩ ከሰኞ ጀምሮ እንደሚቀረፍም አስታውቀዋል፡፡
ኢትዮ ቴሌኮም ከ89 ዋና የካርድ አከፋፋዮች፣ 600 ንኡስ አከፋፋዮችና ከ120 ሺህ ቸርቻሪዎች ጋር የገበያ ትስስር በመፍጠር ካርዶቹን ለተጠቃሚዎች እንደሚያደርስ ሃላፊው አስረድተዋል፡፡  
ከሠሞኑ በአዲስ አበባ በርካታ አካባቢዎች ባለ 5 እና ባለ 10 ብር የሞባይል ካርዶችን ለማግኘት አስቸጋሪ እንደነበር ለአዲስ አድማስ አስተያየታቸውን የሠጡ ተጠቃሚዎች አስታውቀዋል፡፡ መልማይና ላኪ ድርጅቶች ከኢትዮጵያ መንግስት የሥራ ፈቃድ አግኝተው ሠራተኞቹን ለመላክ በዝግጅት ላይ ናቸው ተብሏል፡፡ ወኪሎቹ በአሁኑ ወቅት ሰራተኞቹን ወደ ሣኡዲ ለመላክ የሣውዲ መንግስት ይሁንታ ብቻ እየተጠባበቁ መሆኑን ተገልጿል፡፡  
በቤት ሠራተኝነት የሚላኩት ወጣቶች በቤት አያያዝና ተያያዥ ሙያዎች በቂ ስልጠና እንደተሰጣቸውና ስለ ሣኡዲ ባህልና አኗኗርም ግንዛቤ እንዳገኙም ታውቋል፡፡
ወርሃዊ ደሞዛቸውም 800 የሳኡዲ ሪያል መሆኑን የጠቀሰው ዘገባው፤ የመጀመሪያ የስራ ውላቸው ለ3 ወራት የሚቆይ ሆኖ፤ በሂደት ይራዘማል ተብሏል፡፡
በቅርቡ የኢትዮጵያ ሠራተኛና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴርና የሣኡዲ መንግስት የሠራተኛ ጉዳይ ሚኒስቴር በቤት ሠራተኞች ጉዳይ ስምምነት መፈራረማቸው ይታወሳል፡፡
በዚህ ስምምነት ከተካተቱት ጉዳዮች መካከል የሣኡዲ መንግስት ለሠራተኞች ተገቢውን ጥበቃ እንዲያደርግ፣ ሰራተኞች በህጋዊ ኤጀንሲዎች ብቻ መላክ እንዳለባቸው፣ የኢትዮጵያ መንግስት ለሠራተኞች በቂ ስልጠና ሰጥቶና ጤንነታቸው የተሟላና ለስራ ብቁ መሆናቸውን አረጋግጦ እንዲልክ የሚሉት ይገኙባቸዋል፡፡
በጉዳዩ ላይ ተጨማሪ መረጃ እንዲሰጡን የጠየቅናቸው የሠራተኛ እና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር የህዝብ ግንኙነት ሃላፊ አቶ ግርማ ሸለመ፤ በሳኡዲ ጋዜጣ የወጣው መረጃ በሳኡዲ የተገኘ እንጂ ከኢትዮጵያ መንግስት በኩል የቀረበ አለመሆኑን ጠቅሰው ብዙም ስለጉዳዩ መረጃ የለንም ብለዋል፡፡ በስምምነቶች መሠረት እየተከናወኑ ያሉ ዝግጅቶች መኖራቸውንም ኃላፊው አክለው ገልፀዋል፡፡

Read 3334 times