Saturday, 03 June 2017 00:00

‹‹የማይረሳ ውለታ›› መፅሀፍ ዛሬ ይመረቃል

Written by 
Rate this item
(0 votes)

 በደራሲ አበበ ዓለማየሁ የተፃፈውና በኩባና በኢትዮጵያ ህዝብና መንግስት መካከል ያለውን የግንኙነት ደረጃ ለኢትዮጵያ ህዝብ ያስተዋውቃል የተባለው ‹‹የማይረሳ ውለታ›› መፅሀፍ ዛሬ ጠዋት ከ2፡30 ጀምሮ በብሄራዊ ቴአትር አዳራሽ ይመረቃል፡፡
   መፅሀፉ በዋናነት በወራሪው የሶማሌ ጦር አገር ስትወረር አገራችንን ለመደገፍ የመጡትን የኩባ ወታደሮችና የከፈሉትን መስዋዕትነት እየዳሰሰ ኢትዮጵያውያን ተማሪዎች ኩባ ሄደው በመማር አገራቸውን እንዴት እያገለገሉ እንዳሉና የሁለቱ አገራት መንግስታት ህዝቦች ያላቸውን የጠበቀ የወዳጅነት ግንኙነት ያሳያል ተብሏል፡፡ አንድ የስነ ፅሁፍ ባለሙያም በመፅሀፉ ዙሪያ ዳሰሳ ያቀርባል ተብሏል፡፡ መፅሀፉ በ232 ገፆች ተቀንብቦ፣ በ100 ብር ለገበያ ቀርቧል፡፡ ደራሲው አቶ አበበ አለማየሁ ካሳ ኩባ ሄደው እንዲማሩ እድል ካገኙት የዘመኑ ተማሪዎች አንዱ እንደነበሩ
በመፅሀፉ ጀርባ ባሰፈሩት ማስታወሻ ገልፀዋል፡፡

Read 685 times