Saturday, 11 March 2017 12:07

‹‹አማርኛ ሰዋሰው እና ሥነ ፅሁፍ›› ዛሬ ይመረቃል

Written by 
Rate this item
(0 votes)

 በደራሲ ጋዜጠኛና መምህር የኑስ መሐመድ የተዘጋጀው ‹‹አማርኛ ሰዋሰው እና ሥነ ፅሁፍ›› የተሰኘ
በአማርኛ ሰዋሰው፣ በስነ-ፅሁፍ አለባውያንና መሰል ጉዳዮች ዙሪያ የሚያጠነጥነው መፅሀፍ ዛሬ ከቀኑ 11፡00 ጀምሮ በራስ ሆቴል ይመረቃል፡፡
   በምረቃ ስነ ስርዓቱ ላይ ደራሲያን፣ የኪነ-ጥበብ ባለሙያዎችና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች የሚታደሙ ሲሆን በመፅሀፉ ላይ ዳሰሳ እንደሚካሄድና የስነ - ፅሁፍ ባለሙያዎች ስራዎቻቸውን እንደሚያቀርቡ ታውቋል፡፡

Read 2876 times