Monday, 27 February 2017 07:59

ደ/ ኮርያ በሞባይል ኢንተርኔት ፍጥነት ከአለም 1ኛ ናት ተባለ

Written by 
Rate this item
(1 Vote)

     ደቡብ ኮርያ በሞባይል ኢንተርኔት አገልግሎት ፍጥነት ከአለማችን አገራት የመጀመሪያውን ደረጃ መያዟን ኦፕንሲግናል የተባለው የቴሌኮም መረጃ ተቋም ሰሞኑን ያወጣውን የጥናት ውጤት ጠቅሶ ሲቢሲ ኒውስ ዘግቧል። ተቋሙ በ87 የአለማችን የተለያዩ አገራት የ2016 የፈረንጆች አመት የሞባይል ኢንተርኔት አገልግሎት ፍጥነት ዙሪያ ባደረገው ጥናት፣ ከአለም አንደኛ ደረጃን በያዘቺው ደቡብ ኮርያ የሞባይል ኢንተርኔት ፍጥነት በሰከንድ 37.54 ሜጋ ባይት እንደሚደርስ አስታውቋል፡፡
በሰከንድ 34.77 ሜጋ ባይት ፍጥነት ያለባት ኖርዌይ በሞባይል ኢንተርኔት አገልግሎት ፍጥነት ሁለተኛ ደረጃን መያዟን የጠቆመው ዘገባው፣ ሃንጋሪ በ31.04 ሜጋ ባይት በሰከንድ ፍጥነት ሶስተኛ ደረጃ ላይ መቀመጧን እንዲሁም ሲንጋፖር እና አውስትራሊያ በቅደም ተከተላቸው አራተኛና አምስተኛ ደረጃን መያዛቸውን ገልጧል፡፡
በጥናቱ ከተካተቱት የአፍሪካ አገራት በሞባይል ኢንተርኔት ፍጥነት አንደኛ ደረጃን የያዘቺው ደቡብ አፍሪካ ስትሆን፣ በሰከንድ 9.93 ሜጋ ባይት ፍጥነት ያላት አገሪቱ ከአለማችን አገራት ደግሞ የ48ኛ ደረጃን ይዛለች ተብሏል፡፡

Read 1707 times