የደራሲ፣ አርታኢና ሀያሲ ዓለማየሁ ገላጋይ ልብ ወለድ ‹‹በፍቅር ስም›› የፊታችን ሰኞ ከቀኑ 11፡ 30 ጀምሮ በብሔራዊ ቴአትር አዳራሽ ይመረቃል፡፡ በምረቃው ሥነ-ሥርዓት ላይ ኢ/ር ጌታሁን ሄራሞ፣ ቴዎድሮስ አጥላውና አሸናፊ መለሰ በመፅሐፉ ላይ ዳሠሳ የሚያቀርቡ ሲሆን በሀይሉ ገ/እግዚአብሔር - ወግ፤ ገጣሚ ኤፍሬም ስዩም - ግጥም እንደሚያቀርቡ የፕሮግራሙ አዘጋጅ ‹‹ተረት ፊልሞች›› አስታውቋል። መድረኩን የሚመራው ጋዜጠኛ ደረጀ ሀይሌ ነው
ተብሏል፡፡ ‹‹በዕለቱም በመፅሃፉ ሁለንተና ላይ ውይይት ይካሄዳል፡፡ እርስዎ መፅሃፉን ካላነበቡ እንብበው፣ ካነበቡ ተዘጋጅተው፣ እንዲያም ሲል እኔ ያነበብኩት የደራሲውን ቀደምት ልቦለዶች ነው ካሉ የመወያያ መድረኩ እርስዎንም ያሳትፋልና እንዳይቀሩብን›› ብሏል-ደራሲው በጥሪ ካርዱ ላይ ባሰፈረው ማስታወሻ፡፡
Published in
ኪነ-ጥበባዊ ዜና