በኢትዮጵያዊ ፕሮፌሽናል የአደን ባለሙያ የተሰራውና ከ17 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ ተደርጎበታል የተባለው “ጉዛራ ሆቴል” ዛሬ ይመረቃል፡፡በአደን ሙያ ከዱር እንስሳት ጥበቃ ባለስልጣን ሙሉ ፈቃድ ተሰጥቶአቸው ለረዥም አመታት በሙያው ሲሰሩየቆዩት አቶ ተሾመ አደም፤ በቱሪዝም ዘርፉ ለዓመታት ያዳበሩትን ዕውቀትና ልምድ ተጠቅመው፣ የቱሪስቱን ፍላጎት ለማሟላት በሚያስችል መልኩ ሆቴሉን መስራታቸውን ተናግረዋል፡፡ሲኤምሲ ስዓሊተ ምህረት አካባቢ የተሰራውና ከ20 ለሚበልጡ ኢትዮጵያውያን የሥራ ዕድል ፈጥሯል የተባለውይኸው ሆቴል፤ ዛሬ ታላላቅ የመንግስት ባለስልጣናት በሚገኙበት እንደሚመረቅ ተገልጿል፡፡