Sunday, 29 January 2017 00:00

የዘላለም ጥግ

Written by 
Rate this item
(0 votes)

(ዝነኞች በመሞቻቸው ሰዓት)
‹‹መጋረጃውን አውርዱት- ቧልቱ አብቅቷል››
ፍራንሶይስ ራቤላይስ (ፈረንሳዊ ፈላስፋና ኮሚክ)
“ዕድሜህን ሙሉ ሳትፀልይ በመጨረሻ ሰዓት መፀለይ ዋጋ የለውም!››
ኢታሎ ስቬቮ (አይሁዳዊ ደራሲ)
‹‹መኖር እፈልጋለሁ፤ ምክንያቱም ልሰራቸው የምፈልጋቸው ጥቂት ነገሮች አሉ››
አኔዩሪን ቤቫን
 (በመጨረሻ የህመሙ ሰዓት የተናገረው)                      
‹‹እግዚአብሄር ይቅር ይለኛል፡፡ ምክንያቱም ሥራው ነው››
ሔይንሪክ ሄይን
‹‹የደስታ ዘመኔ አክትሟል››
 (ጄምስ ዲን
የመኪና አደጋ ሊደርስበት ሲል የተናገረው)
‹‹ስንት ሰዓት ነው? ተዉት፡፡ አስፈላጊ አይደለም..››
ጃኖስ አራኒ  (ሃንጋሪያዊ ገጣሚ)
‹‹እንደ ፈላስፋ ኖሬአለሁ፤እናም እንደ ክርስትያን እሞታለሁ››
ኒያኮም ካሳኖቫ (ጣልያናዊ ጀብደኛና ደራሲ)
“ወደ ትውልድ ስፍራዬ ውሰዱኝ። የተወለድኩት ደቡብ ነው፡፡ መሞትና መቀበር የምሻውም ደቡብ ነው”
ቡከር ቲ. ዋሺንግተን
“ደህና ሁኚ … ከተገናኘን …”
ማርክ ትዌይን (ለሴት ልጁ ለክላራ የተናገረው)
(አሜሪካዊ ደራሲ)
“በመንግስተ ሰማያት ስዕል እንደሚኖር፣ በሙሉ ልቤ ተስፋ አደርጋለሁ”
ዣን-ባፕቲስቴ- ካሚሌ ኮሮት (ፈረንሳዊ ሰዓሊ)
“ቡና ስጡኝ፤ ልፅፍ ነው”
ኦላቮ ቢላክ (ብራዚላዊ ገጣሚ)
“ሚላን፡ ለመሞት እንዴት ያለ ውብ ሥፍራ ነው”
ጆን ካራዲን (አሜሪካዊ የፊልም ተዋናይ)
“ከእናንተ ውስጥ ለሰይጣን መልዕክት ያለው ካለ፣ ለእኔ ይስጠኝ፤ አሁን ላገኘው መሄዴ ነው”
ላቪና ፊሸር (በነፍስ ማጥፋት በስቅላት የተቀጣች)
“እዚህ ህመም ይሰማኛል”
ቻርልስ ደ ጎል (የፈረንሳይ መሪ)

Read 1992 times