Saturday, 31 December 2016 11:09

የአፍሪካ የፅንስና ማህፀን ሃኪሞች ጉባዔ ሊካሄድ ነው

Written by 
Rate this item
(3 votes)

የኢትዮጵያ የፅንስና ማህፀን ሃኪሞች ማህበር 25ኛ ዓመቱን ያከብራል

የአፍሪካ ፅንስና የማህፀን ሐኪሞች ፌዴሬሽን ጉባዔ፣ በመጪው የካቲት ወር በአዲስ አበባ ከተማ ውስጥ ሊካሄድ ነው፡፡  ‹‹ዘላቂ የልማት ግቦች በአፍሪካ የስነ ተዋልዶ ጤና፣ ዕድሎችና ተግዳሮቶች›› ‹‹በሚል መሪ ሃሳብ በሚካሄደው በዚሁ አህጉር አቀፍ ጉባኤ ላይ የተለያዩ ጥናታዊ ፅሁፎች ይቀርባሉ፡፡
የአፍሪካ የፅንስና ማህፀን ሐኪሞች ፌዴሬሽን መስራችና አባል የሆነው የኢትዮጵያ ፅንስና ማህፀን ሃኪሞች ማህበር (ኢሶግ)፤ የተመሰረተበትን 25ኛ ዓመት በአሉን ያከብራል፡፡ ይህንኑ የማህበሩን የብር ኢዮቤልዩ በዓልና አህጉር አቀፍ ጉባዔውን እስመልክቶ ማህበሩ በነገው ዕለት በሒልተን ሆቴል ጋዜጣዊ መግለጫ እንደሚሰጥ ማህበሩ ለአዲስ አድማስ የላከው መረጃ ያመለክታል፡፡ በዚሁ ዕለትም የማህበሩ አባላት የሆኑ የህክምና ባለሙያዎች ደም እንደሚለግሱ ታውቋል፡፡


Read 1043 times