Sunday, 25 December 2016 00:00

የግብፅ ክፍተኛ ባለስልጣን በህዳሴው ግድብ ላይ የተደረሰው ስምምነት ውድቅ እንዲሆን ጠየቁ

Written by  አለማየሁ አንበሴ
Rate this item
(14 votes)

     የግብፅ ረዳት የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አምባሳደር ኢብራሂም ዮስሪ፤ በህዳሴው ግደብ ላይ ሀገራቸው ከኢትዮጵያና ከሱዳን ጋር  የደረሰችበት ስምምነት ውድቅ እንዲሆን ለሀገሪቱ የመንግስት ም/ቤት የህግ መሟገቻ አቀረቡ፡፡ አምባሳደሩ፤ ኢትዮጵያ፣ ግብፅና ሱዳን በአባይ ጉዳይና በህዳሴው ግድብ ዙሪያ የተፈራረሙት ስምምነት የግብፅን ህገ መንግስት የሚቃረንና የሀገራቸውን ጥቅም የሚጎዳ መሆኑን እንደገለፁ “ዘ ሚድል ኢስት ሞኒተር” ጋዜጣ ዘግቧል፡፡ የቀረበው የመሟገቻ ሀሳብ ስምምነቱ ግብፅን የሚጎዳ መሆኑን ጠቁሞ፤ “ይህ ስምምነት በግብፅ ፕሬዚዳንት ዙሪያ ያሉ የህግና አለማቀፍ አማካሪዎች ደካማና ለሀገራቸው ጥቅም የቆሙ አለመሆናቸውን ያመለክታል” ብለዋል አምባሳደሩ፡፡ ግንባታው እየተፋጠነ የሚገኘው ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብን በተመለከተ የኢትዮጵያ መንግስት ከሁለቱ ሀገራት ጋር የተለያዩ ውይይቶችን እያደረገ መሆኑ የሚታወቅ ሲሆን ግድቡ በሁለቱ ሀገራት ላይ ምንም አይነት አሉታዊ ተፅዕኖ እንደማይኖረው በተደጋጋሚ መግለፁ አይዘነጋም፡፡

Read 6656 times