Sunday, 09 October 2016 00:00

ዚምባቡዌ በአመት ከ1 ቢ ዶላር በላይ በሙስና እያጣች ነው

Written by 
Rate this item
(1 Vote)

- ቀንደኞቹ ሙሰኞች የመንግስት ባለስልጣናት ናቸው ተብሏል
             
       ዚምባቡዌ በተለያዩ የሙስና ወንጀሎች ሳቢያ በአመት ከ1 ቢሊዮን ዶላር በላይ ገንዘብ እያጣች እንደምትገኝና ከፍተኛውን የሙስና ወንጀል የሚፈጽሙት የመንግስት ባለስልጣናትና የፖሊስ አባላት መሆናቸውን ሮይተርስ ዘገበ፡፡
ትራንስፓረንሲ ኢንተርናሽናል የተባለው አለማቀፍ ተቋም ሰሞኑን ያወጣውን ሪፖርት ጠቅሶ ዘገባው እንዳለው፣ በትምህርትና በትራንስፖርት እንዲሁም በሌሎች ዘርፎች የሚሰሩ የአገሪቱ የመንግስት ባለስልጣናት፣  የሥራ ሃላፊዎችና የፖሊስ አባላት፣ ዜጎችን በከፋ ሙስና እያሰቃዩ ይገኛሉ፡፡ በዚምባቡዌ የሙስና ተግባር ተቋማዊ እየሆነና የበለጠ እየረቀቀ መምጣቱን የጠቆመው ሪፖርቱ፤ የአገሪቱ ተቃዋሚ ፓርቲዎች በከፍተኛ ደረጃ የሚከናወኑ የሙስና ወንጀሎችን መከላከል አልቻሉም ብሏል፡፡ በዚህም የውጭ ኩባንያዎች ሙስናን በመፍራት ወደ አገሪቱ እንዳይገቡ ሆነዋል  በማለት ፕሬዚዳንት ሙጋቤን ተጠያቂ እንደሚያደርጉም ተጠቁሟል፡፡
ፕሬዚዳንት ሙጋቤ፤ ምንም እንኳን ሚኒስትሮቻቸው በሙስና ላይ እንደተሰማሩ በተደጋጋሚ ቢያምኑም አንዳቸውንም ለፍርድ ለማቅረብ አለመሞከራቸውን የሚያረጋግጡ መረጃዎች መገኘታቸውን ዘገባው ያመለክታል፡፡

Read 1372 times