በታደሰ ፀጋ ወ/ስላሴ የተፃፈውና “የመናፍስቱ መንደር” የተሰኘው መፅሐፍ ሰሞኑን ገበያ ላይ ውሏል፡፡ መፅሀፉ በዋናነት በአይን የማይስተዋሉ ስውራን መናፍስትንና የሰዎችን ዘመናት ያስቆጠረ ህቡዕ እንቅስቃሴ አሻራን በስፋት ያስቃኛል ተብሏል። በሰንሰለታማው የሰሜን ተራሮች የሰፈሩ ጥንታዊ ህዝቦች ስልጣኔ፣ባህላዊና መንፈሳዊ ቅርስ እንዲሁም ያልተነገሩ ድብቅ ታሪኮችም በመጽሐፉ ተዳስሷል። በ10 ምዕራፎች ተከፋፍሎ በ275 ገጾች የተቀነበበው መፅሐፉ፤በ77 ብር ለገበያ ቀርቧል፡፡ መጽሐፉን የሚያከፋፍለው እነሆ መፅሐፍ መደብር እንደሆነ ታውቋል፡፡
Published in
ኪነ-ጥበባዊ ዜና