Monday, 08 August 2016 05:33

የኢትዮ-ኬንያ የኤሌክትሪክ ሃይል ማስተላለፊያ ግንባታ ተጀመረ

Written by 
Rate this item
(10 votes)

    ኢትዮጵያ ለኬንያ የኤሌክትሪክ ሃይል ለመሸጥ የያዘቺው እቅድ ዋነኛ አካል የሆነውና 1.2 ቢሊዮን ዶላር ወጪ የሚደረግበት የኤሌክትሪክ ሃይል ማስተላለፊያ መስመር ግንባታ በዚህ ሳምንት መጀመሩን ስታንዳርድ ሚዲያ ዘገበ፡፡1 ሺህ 45 ኪሎ ሜትር ርዝመት ያለውንና 2 ሺህ ሜጋ ዋት የኤሌክትሪክ ሃይል የማስተላለፍ አቅም እንዳለው የተነገረለትን የዚህን የማስተላለፊያ መስመር ግንባታ የሚያከናውነው ቻይና ኤሌክትሪክ ፓዎር ኢኩፒመንት ቴክኖሎጂ የተባለው ኩባንያ እንደሆነ የጠቆመው ዘገባው፣ ግንባታው በታህሳስ ወር 2018 ይጠናቀቃል ተብሎ እንደሚጠበቅ ገልጿል፡፡ኬንያ ከኢትዮጵያ 400 ሜጋ ዋት የኤሌክትሪክ ሃይል ለመግዛት ስምምነት መፈጸሟን የዘገበው ሱዳን ትሪቢዩን በበኩሉ፣ በቀጣይም የምትገዛውን የኤሌክትሪክ ሃይል መጠን በብዙ እጥፍ ለማሳደግ ማሰቧን አስነብቧል፡፡በሁለቱ አገራት መካከል የሚዘረጋው ይህ የኤሌክትሪክ ሃይል ማስተላለፊያ መስመር፣ በ2018 ዓ.ም ለ870 ሺህ አወዎራዎች የኤሌክትሪክ ሃይል አቅርቦት ያሟላል ተብሎ እንደሚጠበቅ የአፍሪካ ልማት ባንክ ማስታወቁንም ዘገባው ጠቁሟል፡፡
በተያያዘ ዜናም ግልገል ጊቤ ሶስት የኤሌክትሪክ ሃይል ማመንጫ ግድብ፣ 800 ሜጋ ዋት ሃይል ማመንጨት መጀመሩን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ሃይል ዋና ስራ አስፈጻሚ ኢንጂነር አዜብ አስናቀ ተናግረዋል፡፡
የግልገል ጊቤ ሶስት የኤሌክትሪክ ሃይል ማመንጫ ግድብ ግንባታ፤ 96 በመቶ እንደደረሰም ኢንጂነር አዜብ አስታውቀዋል፡፡

Read 1785 times