Saturday, 30 July 2016 11:09

የኢትዮጵያ ፖስታ አገልግሎት ድርጅት፤ በህንጻዎች ተንበሸበሸ

Written by 
Rate this item
(2 votes)

• ከ60 ሚ.ብር በላይ በሆነ ወጪ ያስገነባቸውን 4 ህንጻዎች ተረክቧል
• የአዲስ አበባን ጨምሮ በ4 ከተሞች ተጨማሪ ህንፃዎች እያስገነባ ነው

  የኢትዮጵያ ፖስታ አገልግሎት ድርጅት የአገልግሎት መስጪያ ጣቢያዎችን ደረጃ ለማሳደግ ባስቀመጠው መርሐ ግብር መሰረት፤ በተለያዩ የሀገሪቱ ክፍሎች ህንፃዎችን በማስገንባት ላይ ሲሆን በአራት ከተሞች ከ60 ሚ. ብር በላይ በሆነ ወጪ ያስገነባቸውን ህንፃዎች መረከቡን አስታውቋል፡፡ በአርባ ምንጭ ባለ ሁለት ወለል፤ በወልቂጤ፣ በነቀምትና በወሊሶ ከተሞች ባለ ሦስት ወለል ህንፃዎች ነው፤የፖስታ አገልግሎት ድርጅት ያስገነባው፡፡
በተጨማሪም በአዲስ አበባ በቱሪስት ሆቴል አካባቢ ባለ አራት ወለል፤ በሽሬ ባለ ሦስት ወለል፣ በደብረ ታቦር ባለ  ሦስት ወለል፣ በወልዲያ ባለ ሦስት ወለል ህንፃ በአጠቃላይ በ45 ሚ. ብር የ4 ሕንፃዎች ግንባታ በማካሄድ ላይ የሚገኝ ሲሆን ግንባታዎቹ በመጪው ዓመት ይጠናቀቃሉ ተብሎ ይጠበቃል፡፡ በተመሳሳይ፤በአዳማ ባለ ሰባት ወለል፣ በአሰላ ባለ አምስት ወለል፣ በጂግጂጋ ባለ አራት ወለል ህንጻዎችን ለማስገንባትም በዝግጅት ላይ መሆኑን ያስታወቀው ድርጅቱ፤በቀጣይም በአዲግራት፣ በዝዋይ፣ በአላማጣና በአሰበ ተፈሪ ከተማዎች የሕንፃ ግንባታ ለማካሄድ ማቀዱን ጠቁሟል፡፡  
ርክክብ የተፈጸመባቸውም ሆነ በግንባታ ላይ ያሉ ህንጻዎች፤ድርጅቱ ለህብረተሰቡ በሚሰጠው ዘርፈ ብዙ አገልግሎቶች ተደራሽነቱን ለማስፋት ያስችለዋል ተብሏል፡፡

Read 3958 times