Saturday, 02 July 2016 12:42

በዲያቆን ዳንኤል ክብረት የተዘጋጀው አዲስ መጽሐፍ ታትሞ ለንባብ በቃ

Written by 
Rate this item
(3 votes)

   ለታሪክና ለባህላዊ ጥናቶች ትልቅ ዋጋ ያለው ሥራ፤ የተባለለት ‹‹እጨጌ ዕንባቆም - ከየመን እስከ ደብረ ሊባኖስ›› በሚል ርእስ በዲያቆን ዳንኤል ክብረት የተዘጋጀው አዲስ መጽሐፍ ታትሞ በያዝነው ሳምንት ለንባብ በቅቷል፡፡ ብዙ ምስቅልቅል፣ ጦርነቶች፣ ከፍተኛ የሕዝቦች እንቅስቃሴና መፈናቀል የተከሠተበትን የኢትዮጵያን የ16 ኛውን ክፍለ ዘመን ታሪክና አስተዳደራዊ መልክዓ ምድር (ጂኦግራፊ) ለመረዳት ያስችላል የተባለው ይኸው መጽሐፍ፤
ዋጋው ብር 60.00 ሲሆን፤ በመጪው ሳምንት ቅዳሜ (ሐምሌ 9) ከሰዓት በኋላ ከ 8፡30 እስከ 12፡00 ሰዓት፤ በዋቢ ሸበሌ ሆቴል አዳራሽ የታሪክ ምሁራንና ተጋባዥ እንግዶች በተገኙበት እንደሚመረቅ ተገልጿል፡፡ አዲሱ ጽሐፍ የዲያቆን ዳንኤል ክብረት 23ኛ ሥራ መሆኑ ታውቋል፡፡ ዲያቆን ዳንኤል የአዲስ አድማስ ቋሚ አምደኛ መሆናቸው ይታወቃል፡፡

Read 3491 times