Saturday, 02 July 2016 12:26

“የጥበብ መዓዛ” የኪነ- ጥበብ ምሽት ይካሄዳል

Written by  ናፍቆት ዮሴፍ
Rate this item
(1 Vote)

     በጣይቱ የባህል ማዕከል በየዓመቱ የሚዘጋጀውና የአገሪቱን ሥነ-ፅሁፍ ማበረታታት ዋና አላማው አድርጐ የሚንቀሳቀሰው የኪነ- ጥበብ ምሽት የፊታችን አርብ ሀምሌ 1 ቀን 2008 ዓ.ም “የጥበብ መዓዛ” በሚል ርእስ ከቀኑ 10፡30 ሰዓት ጀምሮ በአክሱም ሆቴል ይካሄዳል፡፡በእለቱ ገጣሚ ሄኖክ ስጦታው፣ አዳም ሁሴን፣ በላይ በቀለ ወያ፣ ወሰንሰገድ ገ/ኪዳን፣ የምስራች ግርማ፣ ተክሉ ያለው፣ ሰይፉ ወርቁና ዳዊት ህሩይ ግጥሞቻቸውን ለታዳሚ የሚያቀርቡ ሲሆን በሙዚቀኛ ታምሩ ንጉሴ ይታጀባሉም ተብሏል፡፡ በተጨማሪም በመጋቤ ሐዲስና ሮዳስ ታደሰ “የህዋና የሥነ-ከዋክብት ጥናት በቀደምት ኢትዮጵያዊያን” የተሰኘ ጥናታዊ ገለፃ የሚካሄድ ሲሆን “ሁሉም በአገር ነው” የተሰኘ ዲስኩር በንግድ አመራር ባለሙያውና በአነቃቂ ንግግር አቅራቢው አቶ ሽመልስ ታደሰ እንደሚቀርብ አዘጋጆቹ ገልፀዋል፡፡ “የጥበብ መዓዛ” የኪነ-ጥበብ ምሽት በተመሳሳይ ሳምንት የአሜሪካ ዋሽንግተን ዲሲ ውስጥም ይካሄዳል ተብሏል፡፡

Read 608 times