Saturday, 11 June 2016 13:16

ሃያሲ አብደላ እዝራ ሰኞ በዋቢ ሸበሌ ሆቴል ይዘከራል

Written by 
Rate this item
(26 votes)

ባለፈው ቅዳሜ ድንገት ባደረበት ህመም ከዚህ ዓለም በሞት የተለየውን አንጋፋውን የሥነ ፅሁፍ ሃያሲ አብደላ እዝራን የሚዘክር የኪነ ጥበብ ምሽት ከነገ ወዲያ ሰኞ ከቀኑ 11 ሰዓት ጀምሮ በዋቢ ሸበሌ ሆቴል ይካሄዳል፡፡ በ“ዝክረ አብደላ” የኪነ ጥበብ ምሽት፣ ሃያሲ አብደላ
እዝራ ለአማርኛ ስነ ፅሁፍ ያበረከተው አስተዋፅኦ የሚዳስስ ሲሆን “አብደላና ሂስ”፣ “አብደላና ህይወቱ” በመሳሰሉት ርዕሰ ጉዳዮች ዙሪያ የሥነ ፅሁፍ ባለሙያዎች አስተያየት ይሰጣሉ፡፡
የቅርብ ወዳጆቹም ስለ አብደላ የሚያወቁትን ይመሰክራሉ፤ አብደላን የሚያወድሱ፣ ስራውንና
ሰብዕናውን የሚያወሱ ግጥሞችና ወጎችም ለታዳሚያን ይቀርባሉ ተብሏል፡፡
ይህን የ“ዝክረ - አብደላ” የኪነ ጥበብ ምሽት አዲስ አድማስ ጋዜጣ ያዘጋጀው ሲሆን፣ በምሽቱ አንጋፋና ወጣት ፀሐፍትና ገጣሚያን ስራዎቻቸውን ያቀርባሉ። ከእነዚህም መካከል ነቢይ መኮንን፣ ዶ/ር በድሉ ዋቅጅራ፣ አለማየሁ ገላጋይ፣ ደረጀ በላይነህ፣ ኤፍሬም ስዩም፣ ደምሰው መርሻ፣ ምስራቅ ተረፈ እና ሌሎችም ይገኙበታል፡፡

Read 4562 times