Saturday, 04 June 2016 12:56

በአንድ ሳምንት 1 ሺህ የሜዲትራኒያን ባህር ስደተኞች ሞተዋል

Written by 
Rate this item
(4 votes)

ከጥር ወዲህ ከ2 ሺህ 500 በላይ ሰዎች ለሞት ተዳርገዋል

አለማቀፉ የስደተኞች ተቋም በዚህ ሳምንት በሜዲትራኒያን ባህር ላይ ስደተኞችን አሳፍረው
ሲጓዙ በነበሩ ጀልባዎች ላይ በደረሱ አደጋዎች  አለማቀፉ የስደተኞች ተቋም በዚህ ሳምንት በሜዲትራኒያን ባህር ላይ ስደተኞችን አሳፍረው ሲጓዙ በነበሩ ጀልባዎች ላይ በደረሱ አደጋዎች ለሞት የተዳረጉ የተለያዩ አገራት ዜጎች ቁጥር 1 ሺህ ያህል እንደደረሰ ማስታወቁን ዘ ጋርዲያን ዘገበ፡፡ካለፈው ጥር አንስቶ በሜዲትራኒያን ባህር በደረሱ የጀልባ አደጋዎች ከ2 ሺህ 500 በላይ ስደተኞች ህይወታቸው እንዳለፈ የገለጸው ተቋሙ፤ በአካባቢው በሚከሰቱ አደጋዎች ለህልፈት የሚዳረጉ ሰዎች ቁጥር በከፍተኛ ሁኔታ እያደገ መሆኑን ጠቁሞ፣ በ2014 ተመሳሳይ ወቅት የሞቱት ሰዎች ቁጥር 57 ብቻ እንደነበር አስታውሷል፡፡ በተለይም ከሊቢያ ወደ ጣሊያን የሚዘልቀው የባህር ላይ የጉዞ መስመር እጅግ አስቸጋሪና አደገኛ መሆኑን የጠቆመው ዘገባው፣ አንድ ጀልባ ከመያዝ አቅሙ በላይ እስከ 600 ስደተኞችን በማሳፈር ረጅሙን የባህር ላይ ጉዞ ለማድረግ እንደሚሞክር ገልጾ፣ በተያዘው የፈረንጆች አመት 2016 ብቻ በአካባቢው 2 ሺህ 119 ሰዎች ለህልፈተ ህይወት መዳረጋቸውን አስረድቷል፡፡ወደ አውሮፓ የሚደረገው ስደት እየተባባባሰ መምጣቱን የጠቆመው ዘገባው፤ ካለፈው ጥር ወዲህ 204 ሺህ ስደተኞች ሜዲትራኒያን ባህርን አቋርጠው በሰላም ወደ አውሮፓ መግባታቸውን በመግለጽ፣ ባለፈው አመት ተመሳሳይ ጊዜ አውሮፓ የገቡ ስደተኞች ቁጥር 92 ሺህ ብቻ እንደነበር አስታውሷል፡፡

Read 2405 times