Saturday, 09 April 2016 10:28

ቻይና በሞት ቅጣት ብዙ ሰዎችን በመግደል አለምን ትመራለች

Written by 
Rate this item
(3 votes)

 - ባለፈው አመት በቻይና ከ1ሺህ በላይ ሰዎች ተገድለዋል
              - የሞት ቅጣት የሚፈጸምባቸው ሰዎች ቁጥር ጨምሯል
     አምነስቲ ኢንተርናሽናል የተባለው የሰብዓዊ መብቶች ተሟጋች ድርጅት ባለፈው የፈረንጆች አመት 2015፣ ዜጎችን በሞት በመቅጣት ቻይና ከአለማችን አገራት ቀዳሚውን ስፍራ እንደያዘችና አገሪቱ በአመቱ የሞት ቅጣት የተጣለባቸውን ከ1 ሺህ በላይ ሰዎችን መግደሏን ገለጸ፡፡
ባለፈው አመት 2015 የሞት ፍርዶችን በማስተላለፍና ተፈጻሚ በማድረግ ረገድ በአለማቀፍ ደረጃ ከፍተኛ ጭማሪ ታይቷል ያለው ተቋሙ፣ ቻይናን ሳይጨምር በአመቱ በአለማችን ከ1ሺህ 634 በላይ ሰዎች መገደላቸውንና ካለፈው አመት ጋር ሲነጻጸር ቁጥሩ በግማሽ መጨመሩን መግለጹን ቢቢሲ ዘግቧል፡፡ በአመቱ በኢራን 977 ያህል ሰዎች መገደላቸውን የጠቆመው ዘገባው፣ አብዛኞቹ ሰዎች የተገደሉትም ከአደንዛዥ ዕጽ ጋር በተያያዘ በተመሰረተባቸው ክስ በተላለፈባቸው የሞት ፍርድ ውሳኔ ነው ብሏል፡፡
በ2015 አመት ብቻ በፓኪስታን 326፣ በሳኡዲ አረቢያ 158፣ በአሜሪካ 28፣ በኢራቅ 26፣ በሶማሊያ 25፣ በግብጽ 22፣ በኢንዶኔዢያ 14 እና በቻድ 10 ሰዎች በተለያዩ የወንጀል ክሶች ሳቢያ በሞት መቀጣታቸውንም ዘገባው አክሎ ገልጧል፡፡

Read 1918 times