በዶ/ር መስከረም ለቺሳ የተደረሰውና ከሁለት ዓመት በፊት ለንባብ የበቃው “(ኢ) ዮቶፕያ” የተሰኘው መጽሐፍ ዛሬ ከቀኑ 10 ሰአት፣አምስት ኪሎ በሚገኘው ብሔራዊ የቅርስ ጥናትና ጥበቃ ባለስልጣን አዳራሽ ይመረቃል፡፡ መጽሐፉ በባህል፣ በፍልስፍናና በሃይማኖት ዙሪያ የካበተ ልምድ ባላቸው አንጋፋ ሃያሲያን ተገምግሞም ለውይይት እንደሚቀርብ ታውቋል፡፡
መጽሃፉ፤ለእንግሊዝ መንግስታዊና ሃይማኖታዊ ተሃድሶ ምክንያት የሆነው የመካከለኛው ዘመን የኢትዮጵያ ስርአተ መንግስትንና የህዝቧን አኗኗር የሚያሳይ ነው ተብሏል፡፡ የትርጉም ስራና የምርምር ማስታወሻዎችን ያካተተው መጽሐፉ፤በ348 ገፆች የተቀነበበ ሲሆን ዋጋው 85 ብር ነው፡፡
Published in
ኪነ-ጥበባዊ ዜና