Saturday, 19 March 2016 11:51

የእማሆይ ጽጌ ማርያም ታሪክ በፊልም እየተሰራ ነው

Written by 
Rate this item
(5 votes)

      በኢትዮጵያዊቷ የሙዚቃ ቀማሪና የክላሲካል ፒያኖ ተጫዋች እማሆይ ጽጌ ማርያም ገብሩ የህይወት ታሪክና የሙዚቃ ስራዎች ዙሪያ የሚያጠነጥን አዲስ ፊልም እየተሰራ እንደሚገኝ “ኪክስታርተር” የተባለው ድረገጽ ዘገበ፡፡ በእማሆይ ጽጌ ማርያም የሙዚቃ ፋውንዴሽን እየተሰራ የሚገኘው ይህ ፊልም፣ የ93 አመት የዕድሜ ባለፀጋዋን ያላቸውን የሙዚቀኛ የህይወት ጉዞ የሚያስቃኝ ሲሆን በሙዚቃው ዘርፍ ያላቸውን ተሞክሮና የሙያ ስኬት የሚዳስስ ነው ተብሏል፡፡
በአሁኑ ወቅት በእየሩሳሌም በሚገኝ ገዳም ውስጥ የሚኖሩትን የእማሆይ ጽጌ ማርያም ገብሩን ታሪክ የሚተርከው የዚህ ፊልም የቅድመ ፕሮዳክሽን ስራ መከናወኑን የገለጸው ድረገጹ፤ የፕሮዳክሽን ስራውም በቅርቡ በእየሩሳሌምና ሙዚቀኛዋ በኖሩባቸው የኢትዮጵያ የተለያዩ አካባቢዎች እንደሚካሄድ ገልጿል፡፡
የፊልሙ የድህረ ፕሮዳክሽን ስራ በመጪው ሃምሌ ወር ላይ እንደሚጀመር የተነገረ ሲሆን፣ ፊልሙን በተሳካ ሁኔታ ሰርቶ ለእይታ ለማብቃት ፋውንዴሽኑ ለለጋሾችና ለአጋሮች የገንዘብ እርዳታ ጥሪ ማስተላለፉንም ድረገጹ ባወጣው ዘገባ አስረድቷል፡፡

Read 2849 times