Saturday, 12 March 2016 10:21

ዴንማርክ ኢትዮጵያውያን ህጻናትን በጉዲፈቻ መውሰዷን አቆመች

Written by 
Rate this item
(5 votes)

ኤጀንሲዎች ህጻናትን እየላኩ ገንዘብ በመሰብሰብ ተጠምደዋል ተብሏል
    የዴንማርክ የማህበራዊ ጉዳዮችና የአገር ውስጥ ሚኒስቴር፤ በኢትዮጵያውያ የሚታየው የጉዲፈቻ አሰራር ያልተገባና ህጻናትን ወደ ውጭ አገራት በመላክ ገንዘብ መሰብሰብ ላይ ያተኮረ መሆኑ በጥናት መረጋገጡን ጠቁሞ፣ ከአሁን በኋላ ኢትዮጵያውያን ህጻናትን በጉዲፈቻ ላለመቀበል መወሰኑን አስታውቋል፡፡
“ዘ ኮፐንሃገን ፖስት” የተባለው የአገሪቱ ጋዜጣ እንደዘገበው፣ በኢትዮጵያ ያለው ህጻናትን በማደጎ ወደ ውጭ አገራት የመላክ አሰራር ዴንማርክ በአለማቀፍ የማደጎ ሂደት የምትከተለውን መርህ የማያሟላ ሆኖ በመገኘቱ ውሳኔው ሊተላለፍ ችሏል፤ ሲል ዘግቧል፡፡
በኢትዮጵያ የሚንቀሳቀሱ የጉዲፈቻ አስፈጻሚ ኤጀንሲዎች ወደ ዴንማርክ የሚልኳቸውን ህጻናት በተመለከተ የሚሰጡት መረጃ በአብዛኛው ወጥነት የሌለው ነው ያለው ዘገባው፣ ኤጀንሲዎቹ ትኩረታቸውን ያደረጉት ከውጭ አገራት ኤጀንሲዎች ገንዘብ በመሰብሰብ ላይ መሆኑንና አገራዊ መፍትሄ ከመሻት ይልቅ ህጻናቱን ወደ ውጭ አገራት በማደጎ በመላክ እንደተጠመዱ ጠቁሟል፡፡ በተጠናቀቀው የፈረንጆች አመት 2015 ብቻ በአለማቀፍ የጉዲፈቻ ቅበላ ሂደት 100 ያህል ህጻናት ወደ ዴንማርክ መግባታቸውን ያስታወሰው ዘገባው፤ ከእነዚህ ህጻናት መካከል ሰባቱ ኢትዮጵያውያን መሆናቸውን አስታውቋል፡፡

Read 3359 times