Saturday, 20 February 2016 09:23

ኢትዮጵያና ኬንያ ለሶማሊያ ሰላም አስከባሪ ሂሊኮፕተሮችን ሊሰጡ ነው

Written by 
Rate this item
(12 votes)

     ኢትዮጵያና ኬንያ በሶማሊያ የተሰማራው የአፍሪካ ህብረት ጦር (አሚሶም) ከአልሻባብ ጋር የሚያደርገውን ውጊያ ለማገዝ፣ የጦር ሂሊኮፕተሮችን ሊሰጡ ነው ሲል የኬንያው ዘ ስታር ትናንት ዘገበ፡፡አሚሶም የአልሻባብ ታጣቂዎችን ለመደምሰስ በሚያደርገው ውጊያ፣ ተጨማሪ የጦር መሳሪያዎች አስፈላጊ ሆነው በመገኘታቸው፣ አገራቱ  ሄሊኮፕተሮችን ለማቅረብ መፍቀዳቸውን ዘገባው አስታውቋል፡፡ የሄሊኮፕተሮችና ብዛት ባይገለጽም፣ የሰላም አስከባሪው ወታደሮች በአየር ላይ ድጋፍ እጦት ሳቢያ የገጠሟቸውን እንቅፋቶች ለማስወገድ ያገለግላሉ መባሉን ዘገባው ገልጿል፡፡
ኡጋንዳ ለሰላም አስከባሪው አራት ሄሊኮፕተሮችን ለመስጠት ቃል ገብታ የነበረ ቢሆንም፣ ሶስቱ ሄሊኮፕተሮች በ2012 ወደ ሶማሊያ በመብረር ላይ ሳሉ ከተራራ ጋር ተጋጭተው መከስከሳቸውን ተከትሎ ሃሳቧን መቀየሯንም ዘገባው አስታውሷል፡፡
የሰላም አስከባሪ ወታደሮችን በማሰማራት እንዲሁም የጦር መሣሪያና ቁሳቁስ በማቅረብ፣ ከፍተኛ የውጭ ምንዛሬ የሚያገኙ የአፍሪካ አገራት ኢትዮጵያና ሩዋንዳ እንደሆኑ ዘኢኮኖሚስት መዘገቡ ይታወሳል፡፡

Read 3132 times