Saturday, 20 February 2016 09:17

መንግስት 70 ሺህ ቶን ስንዴ ለመግዛት ጨረታ አውጥቷል

Written by 
Rate this item
(7 votes)

ባለፈው ጥቅምት 1 ሚ. ቶን ስንዴ ለመግዛት ጨረታ አውጥቶ ነበር

   በአንዳንድ አካባቢዎች ድርቅ መከሰቱን ተከትሎ የምግብ እህል ክምችቱን ለማሳደግ እየሰራ የሚገኘው የኢትዮጵያ መንግስት፣ 70 ሺህ ቶን ስንዴ ለመግዛት ሰሞኑን አለማቀፍ ጨረታ ማውጣቱን ኤዢያዋን የተባለው ድረገጽ የአውሮፓ የንግድ ኩባንያዎችን ጠቅሶ ትናንት ዘገበ፡፡መንግስት ግዢውን የሚፈጽመው ከአለም ባንክ አለማቀፍ የልማት ማህበርና ከሌሎች ለጋሾች ባገኘው ገንዘብ እንደሆነ ኩባንያዎቹ መግለጻቸውን የጠቆመው ዘገባው፣ ጨረታው የሚዘጋውም በመጪው ማክሰኞ እንደሆነ መጠቆማቸውን ገልጧል፡፡የኢትዮጵያ መንግስት ባለፉት ወራት ተደጋጋሚ ጨረታዎችን ማውጣቱን ያስታወሰው ዘገባው፣ ባለፈው በጥቅምት ወር 1 ሚሊዮን ቶን ስንዴ ለመግዛት ጨረታ አውጥቶ እንደነበርና የመጨረሻው ጨረታም በጥር ወር መጀመሪያ ላይ 70 ሺህ ቶን ለመግዛት ያወጣው አለማቀፍ ጨረታ እንደሆነ ገልጧል፡፡የዝናብ እጥረት መከሰቱን ተከትሎ በአገሪቱ የምግብና የውሃ እጥረት መከሰቱንና መንግስት የከፋ የምግብ እጥረት ችግር ተጠቂ የሆኑ 10.2 ሚሊዮን ዜጎችን ለመታደግ እየተደረገ ያለውን ጥረት እንዲደግፉ ባለፈው ወር ለአለማቀፍ ለጋሾች ጥሪ ማቅረቡንም ዘገባው አስታውሷል፡፡

Read 1618 times