Saturday, 13 February 2016 12:07

“ዳግማዊት ታይታኒክ” እየመጣች ነው

Written by 
Rate this item
(3 votes)

 የቀድሞዋ  እጣ እንዳይደርስባት፣ የአደጋ መቆጣጠሪያዋ ተሻሽሏል
   ከ104 አመታት በፊት በሰሜን አትላንቲክ ውቅያኖስ በደረሰባት አደጋ በሰጠመችው ታዋቂዋ ታይታኒክ መርከብ ዲዛይን የተሰራችውና ታይታኒክ ሁለተኛ የሚል ስያሜ የተሰጣት አዲስ መርከብ፣ ከሁለት አመት በኋላ መቅዘፍ እንደምትጀምር ዘ ኢንዲፔንደንት ዘገበ፡፡
ብሉ ስታር ላይን የተባለው ታዋቂ ኩባንያ ባለቤት የሆኑት አውስትራሊያዊው ቢሊየነር ክሊቭ ፓልመር ያሰሯት ዳግማዊት ታይታኒክ፣ ከቀድሞዋ ታይታኒክ ጋር ዲዛይኗ ተመሳሳይ ቢሆንም፣ ከዘመኑ የባህር ሃይል ደህንነት መመሪያ ጋር በሚስማማ መልኩ የተወሰነ ማሻሻያ እንደተደረገባት ተነግሯል፡፡
270 ሜትር እርዝማኔ ያላት ዳግማዊት ታይታኒክ፣ ቁመቷ 53 ሜትር ሲሆን ክብደቷም 40 ሺህ ቶን ይደርሳል ተብሏል፡፡ ዘጠኝ ወለሎች ያሏት ሲሆን 2ሺህ መንገደኞችንና 900 የቀዘፋ ሰራተኞችን የመያዝ አቅም እንዳላትም ተነግሯል፡፡ ይህቺኛዋ ታይታኒክ አያድርግባትና የቀድሞዋ ታይታኒክ ክፉ ዕጣ ቢደርስባት፣ የከፋ ጥፋት እንዳይከሰት በሚል በቂ የአደጋ ጊዜ ማምለጫ ጀልባዎች እንድትይዝ ተደርጋለች፡፡ ሌሎች የባህር ላይ አደጋ መቆጣጠሪያና የህይወት አድን መሳሪያዎች በበቂ መጠን የተገጠሙላት ዳግማዊት ታይታኒክ፣ በ2008 መጀመሪያ ጂያንዙ ከተባለችው የምስራቃዊት ቻይና ከተማ ወደ ዱባይ የመጀመሪያዋን ጉዞ ታደርጋለች ተብሎ እንደሚጠበቅም ዘገባው አክሎ ገልጧል፡፡

Read 2111 times