Saturday, 13 February 2016 11:21

“ትንሳኤ ናፋቂዎች መልዕክት ወደ ኢትዮጵያ ሰዎች” መፅሐፍ በጎንደር ይመረቃል

Written by 
Rate this item
(3 votes)

በደራሲ ተስፋ በላይነህ የተፃፈውና በኢትዮጵያ ታሪክ ላይ የሚያተኩረው “ትንሳኤ ናፋቂዎች መልእክት ወደ ኢትዮጵያ ሰዎች” የተሰኘ መፅሀፍ የፊታችን አርብ ከ10 ሰዓት ጀምሮ ጎንደር ከተማ በሚገኘው ላንድ ማርክ ሆቴል ይመረቃል፡፡ አንጋፋው ደራሲና ሀያሲ ዓለማየሁ ገላጋይ፤ በሥፍራው ተገኝቶ በመፅሀፉ ላይ ሂሳዊ ዳሰሳ እንደሚያደርግ የምረቃ አስተባባሪው “ግጥም በመሰንቆ” ገልጿል፡፡ በ302 ገፆች የተቀነበበው መፅሀፉ፤ በ69 ብር ለገበያ ቀርቧል፡፡ ደራሲው ከዚህ ቀደም “የሚንከራተቱ ኮከቦች” የተሰኘ መፅሀፍ ለንባብ ማብቃቱ ይታወሳል፡፡

Read 1005 times