የተለያዩ የአለማችን አገራት አይሲስን ለመደምሰስ በኢራቅና በሶርያ የሚፈጽሙት የአየር ጥቃት ያሰጋቸው በርካታ የሽብር ቡድኑ ከፍተኛ የጦር መሪዎች ከጥቃቱ ሸሽተው ወደ ሊቢያ እየገቡ ነው ሲል ቢቢሲ ዘገበ፡፡
ሊቢያ ለሽብር ቡድኑ አመራሮች ምቹ አገር በመሆኗ፣ በርካታ የተለያዩ አገራት ዜግነት ያላቸው የአይሲስ ከፍተኛ የጦር አበጋዞች ሲርት ወደ ተባለችውና በቡድኑ ቁጥጥር ስር ወደምትገኘው የአገሪቱ ከተማ እየገቡ እንደሚገኙ የሊቢያ የስለላ ተቋም ሃላፊ ኢስማኤል ሹክሪ መናገራቸው ተገልጿል፡፡
ከተማዋ ካለፈው አመት ጀምሮ በአይሲስ ቁጥጥር ስር እንደምትገኝ ያስታወሰው ዘገባው፣ ከቅርብ ወራት ወዲህ ከኢራቅና ከሶርያ ሸሽተው ወደ ሲርት የሚገቡ የሽብር ቡድኑ ከፍተኛ የጦር መሪዎች ቁጥር እየጨመረ እንደሚገኝ አመልክቷል፡፡
በሽሽት ወደ ከተማዋ ከገቡት የቡድኑ አባላት አብዛኞቹ የቱኒዝያ፣ የግብጽና፣ የሱዳን ዜግነት ያላቸው ናቸው ያለው ዘገባው፣ አልጀሪያውያን፣ ኢራቃውያንና ሶርያውያንም እንደሚገኙባቸው የተነገረ ሲሆን፣ በተለይም ለቡድኑ የረጂም ጊዜ የሽብር ተልዕኮ ስኬታማነት ጉልህ ሚና የሚጫወቱ የቡድኑ አባላት ወደ ሊቢያ መሸሻቸውንም ዘገባው አክሎ ገልጿል፡፡
Published in
ከአለም ዙሪያ