Saturday, 06 February 2016 10:35

ወደ ሥራ ያልገቡ የ91 ፕሮጀክቶች ፈቃድ ተሰረዘ

Written by 
Rate this item
(2 votes)

ባለፉት ስድስት ወራት የ91 ፕሮጀክቶችን የኢንቨስትመንት ፈቃድ መሰረዙን የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን

አስታወቀ፡፡
የኮሚሽኑ የህዝብ ግንኙነት ዳይሬክተር አቶ ጌታሁን ነጋሽ ለአዲስ አድማስ እንደተናገሩት፤ ፕሮጀክቶቹ

በማኑፋክቸሪንግ ዘርፍ ለመስራት ፈቃድ ተሰጥቷቸው የነበሩ ሲሆን ፈቃዳቸው የተሰረዘው ፈቃድ ካወጡ በኋላ

በመጥፋትና በሁለት ዓመት ጊዜ ውስጥ ወደ ሥራ ለመግባት ባለመቻላቸው ነው፡፡
የፈቃድ መሰረዙን ተከትሎም መሬት የሰጠው አካል መሬቱን፣ ገንዘብ የሰጠው አካል ገንዘቡን፣ እንዲያስመልስ

እንዲሁም መሳሪያዎችን በነፃ ለማስገባት በሂደት ላይ ያሉም እንዲከለከሉ ኮሚሽኑ ለሚመለከታቸው አካላት ሁሉ

ማሳወቁን ዳይሬክተሩ ጠቁመዋል፡፡
ባለፈው ዓመትም እንዲሁ በማኑፋክቸሪንግና በግብርና ዘርፎች ለመሰማራት ፈቃድ ተሰጥቷቸው በወቅቱ ወደ ስራ

ያልገቡ 357 ፕሮጀክቶች ፈቃዳቸው መሰረዙን አቶ ጌታሁን አስታውሰዋል።
ኮሚሽኑ ባለፈው ሩብ ዓመት 107 አዲስ፣ 23 የማስፋፊያ፣ በድምሩ 130 የኢንቨስትመንት ፈቃዶችን በማኑፋክቸሪንግ፣

በግብርናና በአገልግሎት ዘርፎች የሰጠ ሲሆን ከነዚህ ውስጥም 29ኙ የአገር ውስጥ ባለሀብቶች መሆናቸውን አቶ

ጌታሁን ገልፀዋል፡፡

Read 1197 times