Monday, 11 January 2016 12:08

በተቃጠለ መኖሪያ ቤት ውስጥ ባልና ሚስት ሞተው ተገኙ

Written by  አለማየሁ አንበሴ
Rate this item
(19 votes)

ባል ሚስቱን ገድሎ ራሱን ሳያጠፋ አልቀረም ተብሏል

   በአዲስ አበባ ቦሌ ክ/ከተማ ወረዳ 7 ጃክሮስ አደባባይ አካባቢ በሚገኝና ትናንት ጠዋት የእሣት ቃጠሎ በደረሰበት ቤት ውስጥ ባልና ሚስት ሞተው የተገኙ ሲሆን የሰዎቹ ሞት ከቃጠሎው ጋር የተገናኘ እንዳልሆነ ታውቋል፡፡
የእሣት አደጋ ሠራተኞች በደረሳቸው ጥሪ መሰረት ትናንት ጠዋት 2 ሰዓት ገደማ በስፍራው ደርሰው እሣቱን ያጠፉ ሲሆን ባልና ሚስቱ የቃጠሎ አደጋ ሳይደርስባቸው ሞተው መገኘታቸውን የጠቆሙት የአዲስ አበባ እሣትና ድንገተኛ አደጋ መከላከል የኮሚኒኬሽን ባለሙያ አቶ ንጋቱ ማሞ፤ 30ሺ ብር የሚገመት ንብረት መውደሙንም ገልፀዋል፡፡
ሟቾች የ60 ዓመቱ አቶ ብርሃኑ ቡሌና የ44 ዓመቷ ወ/ሮ አስቴር አሰፋ፤ የ6 ልጆች ወላጆች ሲሆኑ ባል፣ ሚስቱን ገድሎ ራሱን ሳያጠፋ እንዳልቀረ መጠርጠሩን ምንጮች ጠቁመዋል፡፡
የእሣቱ መነሻ ሲሊንደር ነው ያሉት ምንጮቹ፤ ፖሊስ በእሣቱ መነሻና በባልና ሚስቱ አሟሟት ላይ ተጨማሪ ምርመራ እያደረገ መሆኑን አመልክተዋል፡፡

Read 6128 times