Tuesday, 29 December 2015 07:06

ዘንድሮ ከዲያስፖራው ከ3 ቢ. ዶላር በላይ ተልኳል

Written by 
Rate this item
(0 votes)

ገቢው ከኤክስፖርትና ከለጋሾች ከተገኘው በላይ ነው

   በተገባደደው የፈረንጆች አመት 2015 በአለም ዙሪያ ከሚገኙ ኢትዮጵያውያንና ትውልደ ኢትዮጵውያን ወደ አገር ውስጥ የተላከው ገንዘብ 3.7 ቢሊዮን ዶላር መድረሱንና፣ ይህም በዘርፉ ክብረወሰን የተመዘገበበት እንደሆነ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አስታወቀ፡፡
በውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የዲያስፖራ መረጃና ምርምር ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ደመቀ አጥናፉን ጠቅሶ ኤፒኤ እንደዘገበው፣ ኢትዮጵያ ከዚህ ቀደም ይህን ያህል ገንዘብ አግኝታ የማታውቅ ሲሆን፣ ገንዘቡ  በአመቱ ከወጪ ንግድና ከውጭ አገራት ለጋሾች ከተገኘው በላይ እንደሆነ ተረጋግጧል፡፡
ህንድ በ2014 ብቻ ከዘርፉ 70 ቢሊዮን ዶላር ማግኘቷን የጠቀሱት አቶ ደመቀ፤ ኢትዮጵያ በዘርፉ የምታገኘው ገቢ አሁንም አነስተኛ መሆኑን ጠቁመው፣ ከዘርፉ የሚገኘውን በቀጣይ አመታት ለማሳደግ ታቅዶ እየተሰራ መሆኑን ገልፀዋል፡፡

Read 1496 times