Saturday, 19 December 2015 11:05

በሺህዎች የሚቆጠሩ ደ/አፍሪካውያን ፕሬዚዳንቱ ከስልጣን እንዲወርዱ ጠየቁ

Written by 
Rate this item
(0 votes)

 በመላ አገሪቱ የተቃውሞ ሰልፎች ተደርገዋል

ባለፈው ሳምንት ሁለት የፋይናንስ ሚኒስትሮችን ከሃላፊነታቸው ያነሱት የደቡብ አፍሪካው ፕሬዚዳንት ጃኮብ ዙማ፤ የአገሪቱን ኢኮኖሚ የሚያደቅ ተግባር እየፈጸሙ ነው በሚል ባለፈው ረቡዕ አደባባይ ወጥተው ተቃውሟቸውን ያሰሙ በሺህዎች የሚቆጠሩ ደቡብ አፍሪካውያን ፕሬዝዳንቱ ከስልጣን እንዲወርዱ መጠየቃቸውን ቢቢሲ ዘገበ፡፡
በርካታ ደቡብ አፍሪካውያን በአገሪቱ ሙስና ተስፋፍቷል፣ በገዢው ፓርቲ የስልጣን መተካካት ላይ አግባብ ያልሆነ ተግባር ተፈጽሟል በሚል ተቃውሟቸውን ሲያሰሙ መቆየታቸውን ያስታወሰው ዘገባው፣ በሺህዎች የሚቆጠሩ የአገሪቱ ዜጎች ረቡዕ ዕለት ጆሃንስበርግ ውስጥ ባደረጉት የተቃውሞ ሰልፍ ፕሬዚዳንቱ ከስልጣን እንዲወርዱና በመንግስት የሚከናወኑ የሙስና ድርጊቶችን የሚገታ ጠንካራ ንቅናቄ እንደጀመር መጠየቃቸውን አስታውቋል፡፡
በዕለቱ ከጆሃንስበርግ በተጨማሪ በመላ አገሪቱ የተለያዩ አካባቢዎች የተቃውሞ ሰልፎች መደረጋቸውን የጠቆመው ዘገባው፣ በኬፕታውን በተከናወነው ተመሳሳይ የተቃውሞ ሰልፍ የተሳተፉ በሺህዎች የሚቆጠሩ ዜጎች ዙማ ከስልጣን መውረድ አለባቸው የሚል መፈክር ሲያሰሙ መዋላቸውን ጠቁሟል፡፡
ፕሬዚዳንት ጃኮብ ዙማ የቀድሞውን የአገሪቱ የፋይናንስ ሚኒስትር ናላላ ኔኔን ከሃላፊነታቸው ማንሳታቸው ከፍተኛ ትችት እንዳስከተለባቸውና ውሳኔያቸው የገበያ ቀውስ መፍጠሩንም አስታውሷል፡፡

Read 1838 times