Saturday, 28 November 2015 08:56

የቀልድ ጥግ

Written by 
Rate this item
(3 votes)

(በፍቺና ጥርጣሬ ዙሪያ)
ሚስት የቤተሰቡ ጠበቃ ዘንድ ትደውልና
በአስቸኳይ እንደምትፈልገው ትነግረዋለች፡፡
ጠበቃውም ያለችበት ሥፍራ ከመቅጽበት
ይደርስና ለምን እንደፈለገችው ይጠይቃታል፡፡
“ምን ገጥሞሽ ነው እንዲህ በአስቸኳይ
የፈለግሽኝ?”
“ከባሌ ጋር መፋታት እፈልጋለሁ” አለች እሳት
ለብሳ እሳት ጐርሳ፡፡
“ምነው ደህና አልነበራችሁ እንዴ?”
“የመጨረሻ ልጃችን አባት እሱ አይደለም የሚል
ከፍተኛ ጥርጣሬ አለኝ” ብላው እርፍ!!
* * *
አዳም ያለ አመሉ ለተወሰኑ ቀናት ውጭ እያመሸ
በመግባቱ፣ ሄዋን ጥርጣሬ ቢጤ አደረባት፡፡
“እንዳትዋሸኝ…ከሌላ ሴት ጋር መቅበጥ ጀምረሃል
አይደል!?” ስትል ታፋጥጠዋለች፡፡
“የምን ሌላ ሴት ነው የምታወሪው? አንቺው ነሽ
ሌላ ማን አለ!” አዳም ግራ በተጋባ ስሜት መለሰላት፡፡
የዚያኑ ዕለት ሌሊት አዳም ጥልቅ እንቅልፍ ላይ
ሳለ፣ ሄዋን ደረቱ አካባቢ በጣቷ ስትጫነው ባንኖ
ይነሳና፤ “ምን እያደረግሽ ነው?” ይጠይቃታል፡፡
“ጐድንህን እየቆጠርኩ” መለሰችለት፡፡
(አዳም ምን ብሎ ይሆን?

Read 1734 times