Saturday, 07 November 2015 10:25

የዳዊት ጽጌ የምስጋናና የሙዚቃ ዝግጅት ዛሬ ምሽት ይካሄዳል

Written by 
Rate this item
(1 Vote)

      የ2008 ዓ.ም የ“ባላገሩ ምርጥ” የድምፅ ውድድር አሸናፊ አርቲስት ዳዊት ፅጌ፣ በውድድሩ ሂደት ያገዙትንና ከጎኑ የነበሩትን ድርጅቶችና ግለሰቦች የሚያመሰግንበት ልዩ የሙዚቃ ዝግጅት ዛሬ ምሽት ይካሄዳል፡፡ የዝግጅቱ አስተባባሪ እንደሻው የኪነ-ጥበብ ፕሮሞሽን በላከው መግለጫ እንዳስታወቀው፣ ፕሮግራሙ ዛሬ ምሽት በባታ የባህል ምግብ ቤትና መናፈሻ ፓርክ የሚከናወን ሲሆን ምሽቱ ድምፃዊው በውድድሩ ሂደት የረዱትን ድርጅቶችና ግለሰቦች የሚሸልምበትና ከቅላፄ ባንድ ጋር ልዩ የሙዚቃ ዝግጅት የሚያቀርብበት ይሆናል ተብሏል፡፡   
ድምፃዊ ዳዊት ፅጌ በምሽቱ አዲስ የሙዚቃ ስራውን ያቀርባል ተብሎ የሚጠበቅ ሲሆን ከእውቁ የፒያኖ ተጫዋች ግርማ ይፍራሸዋ፣ ከአርቲስት ግርማ ነጋሽ፣ ከአርቲስት ባህታ ገ/ህይወትና ከአርቲስት ግርማ በየነ ጋር በጋራ እንደሚያቀነቅንም እንደሻው የኪነ-ጥበብ ፕሮሞሽን አስታውቋል፡፡ ባታ የባህል ምግብ ቤትና መዝናኛ ፓርክ እና ኢምር አድቨርታይዚንግ የፕሮግራሙ አጋር እንደሆኑ ለማወቅ ተችሏል፡፡  

Read 2513 times