Saturday, 07 November 2015 10:24

የኢትዮጵያ ዓለም አቀፍ ፊልም ፌስቲቫል ሰኞ ይከፈታል

Written by 
Rate this item
(0 votes)

    በሊንኬጅ አርት ሪሶርስ ሴንተር አዘጋጅነት የሚካሄደው 10ኛው የኢትዮጵያ ዓለም አቀፍ ፊልም ፌስቲቫል ከነገ በስቲያ በ11 ሰዓት በኦሮሚያ ባህል ማዕከል ይከፈታል፡፡ እስከ ህዳር 6 ቀን 2008 ዓ.ም ድረስ በሚቆየው የፊልም ፌስቲቫል ላይ ከ70 በላይ የአገር ውስጥና የውጭ አገር ፊልሞች ሳምንቱን ሙሉ እንደሚታዩ የተገለፀ ሲሆን ከአሜሪካ ኤምባሲ ጋር በመተባበር ከአሜሪካ በሚመጡ የፊልም ባለሙያዎች የአንድ ቀን ኮንፍረንስ ይካሄዳልም ተብሏል፡፡ ከዚህም በተጨማሪ ከእስራኤል በሚመጡ የፊልም ባለሙያዎች ለፊልም ሞያተኞች የግማሽ ቀን ስልጠና እንደሚሰጥ የተጠቆመ ሲሆን ህዳር 6 ቀን 2008 ዓ.ም ለአሸናፊ የፊልም ባለሙያዎች ሽልማት በማበርከት ፌስቲቫሉ እንደሚዘጋ አዘጋጁ ሊንኬጅ አርት ሪሶርስ ሴንተር በላከው መግለጫ አስታውቋል፡፡

Read 1756 times