Saturday, 07 November 2015 10:23

“The show must go on” ለእይታ በቃ

Written by 
Rate this item
(0 votes)

    በሪቻርድ ቪያ የተፃፈው “The show must go on” የተሰኘ ድራማ በአርቲስት ፈለቀ የማር ውሃ አበበ “ትርኢቱ ይቀጥላል” በሚል ተተርጉሞና ተዘጋጅቶ ትላንት ምሽት በሃርመኒ ሆቴል ለእይታ በቃ፡፡ የ30 ደቂቃ ርዝማኔ ያለው ይሄው ፋርስ ኮሜዲ ድራማ፤ በኒውዮርክ ዩኒቨርስቲ ማስተማሪያ እንደሆነም ለማወቅ ተችሏል፡፡
በሶል ፕሮሞሽንና በአቶ ሰለሞን ግዛው ፕሮዲዩስ የተደረገው ድራማው፤ በየ15 ቀኑ አርብ በበደሌ ኮሜዲ ምሽት በሃርመኒ ሆቴል ለተመልካች የሚቀርብ ሲሆን አርቲስት ሱራፌል ተካ፣ ሰለሞን ተስፋዬ፣ መስከረም አበራ፣ ሰለማዊት በዛብህ፣ ብሩክ ትንሼ፣ ዳዊት አለሙና ሄኖክ በሪሁን እንደሚተውኑበት ተርጓሚና አዘጋጁ ለአዲስ አድማስ ገልጿል። ድራማው መታሰቢያነቱ ለብሔራዊ ቴአትር 60ኛ ዓመት መሆኑንም አርቲስቱ ተናግሯል፡፡

Read 1882 times