Saturday, 07 November 2015 10:21

“የኔ ቢጤ ሰማይ” ሰኞ በገበያ ላይ ይውላል

Written by 
Rate this item
(2 votes)

    በወጣት ገጣሚ መስፍን ወንድ ወሰን የተጻፈውና 67 ያህል ግጥሞችን ያካተተው “የኔ ቢጤ ሰማይ” የተሰኘ የግጥም ስብስብ መጽሃፍ ከነገ በስቲያ ሰኞ ጀምሮ በገበያ ላይ ይውላል፡፡
ገጣሚ መስፍን በተለይ ለአዲስ አድማስ እንደገለጸው፣ የመጀመሪያ ስራው የሆነውና 100 ያህል ገጾች ያሉት “የኔ ቢጤ ሰማይ” በተለያዩ ርዕሰ ጉዳዮች ዙሪያ የሚያጠነጥኑ ግጥሞች ተካትተውበታል፡፡
የመሸጫ ዋጋው 40 ብር የሆነው መጽሃፉ፣ ከመጪው ሰኞ ጀምሮ በአዲስ አበባና  በክልል ከተሞች በሚገኙ የመጽሃፍት መደብሮችና በአዟሪዎች በገበያ ላይ እንደሚውልም ገጣሚው ለዝግጅት ክፍላችን ገልጿል፡፡

Read 1544 times