በወጣት ገጣሚ መስፍን ወንድ ወሰን የተጻፈውና 67 ያህል ግጥሞችን ያካተተው “የኔ ቢጤ ሰማይ” የተሰኘ የግጥም ስብስብ መጽሃፍ ከነገ በስቲያ ሰኞ ጀምሮ በገበያ ላይ ይውላል፡፡
ገጣሚ መስፍን በተለይ ለአዲስ አድማስ እንደገለጸው፣ የመጀመሪያ ስራው የሆነውና 100 ያህል ገጾች ያሉት “የኔ ቢጤ ሰማይ” በተለያዩ ርዕሰ ጉዳዮች ዙሪያ የሚያጠነጥኑ ግጥሞች ተካትተውበታል፡፡
የመሸጫ ዋጋው 40 ብር የሆነው መጽሃፉ፣ ከመጪው ሰኞ ጀምሮ በአዲስ አበባና በክልል ከተሞች በሚገኙ የመጽሃፍት መደብሮችና በአዟሪዎች በገበያ ላይ እንደሚውልም ገጣሚው ለዝግጅት ክፍላችን ገልጿል፡፡
Published in
ኪነ-ጥበባዊ ዜና