Saturday, 10 October 2015 16:45

“እስኪነጋ ድረስ” በገበያ ላይ ዋለ

Written by 
Rate this item
(3 votes)

 በደራሲ አሳየ ደረበ የተጻፈው “እስኪነጋ ድረስ” የተሰኘ የወጎች፣ የአጫጭር ልቦለዶችና የግጥሞች ስብስብ መጽሃፍ ሰሞኑን በገበያ ላይ መዋሉን ደራሲው በተለይ ለአዲስ አድማስ ገለጸ፡፡
በተለየ አቀራረብ የተሰናዳው መጽሃፉ፤በተለያዩ ማህበራዊ ጉዳዮች ዙሪያ የሚያጠነጥኑ 18 ያህል ወጎችንና አጫጭር ልቦለዶችን የያዘ ሲሆን በታሪኮቹ መካከልም ከታሪኮቹ ሃሳቦች ጋር ተያያዥ የሆኑ 30 ያህል ግጥሞችን አካትቷል፡፡
ደራሲው ለህትመት ያበቃው የመጀመሪያ ስራው የሆነው “እስኪነጋ ድረስ”፤ በአዲስ አበባ እና በክልል ከተሞች በሚገኙ የመጽሃፍት መደብሮችና አዟሪዎች ዘንድ በ50 ብር እየተሸጠ ይገኛል፡፡
ደራሲ አሳየ ደረበ በፌስቡክ ማህበራዊ ድረ-ገጽ አዝናኝና አስተማሪ ወጎችን፣ የግል እይታዎችን፣ ግጥሞችንና የተለያዩ ጽሁፎችን በስፋት በማቅረብና በርካታ አንባብያንና ተከታዮችን በማፍራት የሚታወቅ ሲሆን በቀጣይም ሌሎች የወጎችና የአጫጭር ልቦለድ መጽሃፍትን ለአንባብያን የማድረስ ዕቅድ እንዳለው ለአዲስ አድማስ ተናግሯል፡፡

Read 1956 times